Tuesday, March 12, 2013

     

ዝም ባለ አፍ ዝንብ አይገባም ብለን ዝም ስንል ዝም ባልንበት አፍ ወንጀለኛ ተባልን።


ዝም ባለ አፍ ዝንብ አይገባም ብለን ዝም ስንል ዝም ባልንበት አፍ ወንጀለኛ ተባልን።
አማራ መሆን ወንጀል ነውየሌሎች ብሔረሰብ አባላት በፈለጉበትክልልና ስፍራ ይኖራሉ። አማራ ክልል ውስጥ ሰፊ መሬት ወስደው የሚኖሩአሉ፤ የሚነካቸው የለም። አማራው እየተመረጠ ለስደት፣ ለመከራ፣ለእንግልት ይዳረጋልእስከመቼ በዚህ ይቀጥላል?  የአማራ ክልሉንእንመራለን፣ የአማራ ህዝብ ወኪል ነን የሚሉ የት ናቸውያሳዝናል! ግንወኪሉም ተብዬው ለካ የወያኔ ስራ አስፈፃሚሆች ናቸው ለካ ምን ይደረግለአማራው አልቅሱ፣ ለአማራው አንቡ፣ አማራው አለቀ፣ልጆቻችንየሚቀበለን በጉዲፈቻ እያሉ …”   በስልክ ለተለያዩ ሬዲዮ ጣቢያ በስልክ ሲቃ ልሳናቸው አንቆ  አስተያየታቸው  የአማራ ተወላጆች ሲናገሩ አልሰማንም የሚል የለም ካንም እኔ አይመለከተኝም ሊሆን ይችላል ግን ነገ ደግሞ በሌላው ብሔረሰብ መደገሙ የማይቀር ነውና ዛሬ ይኽንየወያኔን ስራ መቃወም አለብን 
ሰሞኑን በቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል አማራውን የማፅዳት ዘመቻ ወይምየማፈናቀል ዘመቻ መጀመሩ ይፋ ሆነ እንጂ ችግሩ የቆየና ማዕከላዊአገዛዙም ሆነ የክልሉ መስተዳድር ጠንቅቀው የሚያውቁት ጉዳይእንደሆነም ይታወቃል የካቲት 282005  የተላለፈው ኢሳት አማርኛክፍል ያነጋገራቸው የችግሩ ሰለባ አሁን ያለውን ችግር የሚገልጹትበተማጽኖ ነበር
 ከዚህ በፊትም ከዓመታት በፊት መተከል ዞን ፓዌ የተካሄደውን ማስታወስይቻላል 1984 – 85 ፓዌ መንደር አራት በሚባለው የገበያ ቦታእየገበዩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ያላሰቡት ደረሰባቸው።በድንገት ገበያውታወከ። የቻሉትን በቀስት፣ ሌላውን በጥይት ለቀሙት። 56 ሰዎችበቅጽበት ሲረሸኑ ይህ ሁሉ ሲደረግ አገር የሚመሩት ባለስልጣኖችድምጻቸውን አላሰሙም ነበር ሆን ብለው ያደረጉት ስለነበረ።
በጉራፈርዳ በክልሉ መንግስት ትዕዛዝ የከፋ ወንጀል ሲሰራ፣ አንደኛ ክፍልለሚማር ህጻን ጭምር “ክልሉን ልቀቅና ውጣ” የሚል ደብዳቤ ሲሰጥተቆጣጣሪና ተቆርቋሪ አለመኖሩ መጨረሻ የሌለው ግፍ አማራው ላይእንዲካሄድ ስምምነት ያለ የሚገልጹ ጥቂት አይደሉም።
በቤንሻንጉል መተከል ዞን ቡሎን ወረዳ የሰፈሩና 20 ዓመት በላይ ይኖሩየነበሩ ሰዎች በረሃውን አልምተው፣ ወልደው ከብደውና ንብረት አፍርተውይኖሩ የነበሩ አምስት ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከየካቲት19 እስከ 30 ቀን2013 ዓም መኖሪያቸውን ለቀው እንዲወጡ ታዝዘዋል የሚገርመው ግን 20  በላይ የአማራ ተወላጆች የሚኖሩ ሲሆን ቀስ በቀስ የማጣራትዘመቻም እንደሚደረግ ይታወቃል
 የአማራ ተወላጆቹ ሰሚ አጣን”  ድምጻ የሚሰማን አጣን በአገራችንለክልሉ መንግስት ሲናገሩ፣ ሲያመለክቱ አመለከታችሁ በሚልስለምንታሰር፣ስለምንደበደብ እባካችሁ ለፌደራሉ መንግስት አሳውቁልንሲሉ በተለያዩ መገናኛ ተደምጠዋል። አገር ቤት የመንግስትም ሆነ “የግልየሚባሉት የመገናኛ ዘዴዎች ጆሮ የነሷቸው ይመስል ሰምተው ዝምብለዋል። ጥያቄ ያቀረቡት ሰዎች “ፈልሶ የመጣ፣መጤ፣ውጣ አማራእየተባሉ የውጭ አገር ዜጋ እንኳን በማይጠራበት ሁኔታ ክብረ ነክ ስድብእንደሚሰደቡ ተናግረውም ነበር ተበዳዮቹ። የሚያሳዝነው ባፋጣኝ ክልሉንለቀው ካልወጡ የክልሉ መንግስት ባለስልጣናት ምን ሊከሰት እንደሚችልየዛቱባቸውን ሰዎች በሚዲያም ተናግረውም ጭምር ነበር‹በአማርኛ ተናጋሪነታችን ሠርተን የመኖር ልጆቻችንን የማሳደግ ህልውና ያጣን ነን፡፡›› የሚሉት እነዚህ ዜጎች “በተደጋጋሚ ጥቃት እየተሰነዘረብን ነው፤ ከ20 ዓመት በላይ ከኖርንበት መሬት ተፈናቅለናል፡፡ ከአውሬ ጋር እየታገልን ያለማነውን መሬት ተነጥቀናል፡፡ እነሱ የሚሉን እናንተ አማራ ስለሆናችሁ በዚህ ክልል መኖር አትችሉም፡፡ ወደ ክልላችሁ ሂዱ ይሉናል፡፡ አማራ ክልልን እንኳን ሰርተን የምንበላበት መሬት ቀርቶ ጎጆ ቀልሰን የምንኖርበት ቦታ ሊሰጡን ፈቃደኛ አይደሉም፡፡” ባስቸኳይክልሉን ለቀው ካልወጡ “የፌደራል ፖሊስ ደብድቦ ያስወጣሃል” የሚልማስፈራሪያ የደረሳቸው ሰዎች ጭምር ነበሩ።
የአማራ ክልል ለምና ሰፊ መሬቱን ለሱዳን አሳልፎ በመስጠት፣ ሁመራንናወልቃይት ገባውን ለትግራይ ክልል አሳልፎ በማስረከብ የሚታወቀውንብአዴን ዛሬ ዝም ቢል አይገርምም እኮ ከዝንብ ማር ይጠበቃል እንዲ አቶደመቀ መኮንን በአማራው ወያኔ ስም “ቅምጥ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርሆነው በውለታ መሾማቸው የሚታወስ ነው።
ግን ይዄ ሁላ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ዝም ማለቱ ነገ ዋጋ እንደሚያስከፍለውስ ሳያቀው ቀርቶ ነው።መቼም የአማራ ክልል ብአዴን ለምን ዝም አለ አንልም ምክንያቱም የወያኔ ጀሌ፣ሎሌ ሆኖ እያገለገለ ያለ እንጂ ለህዝቡ እያገለገለ እንዳልሆነ ይታወቃል።
ዝም ባለ አፍ ዝንብ አይገባም ከሆነ ታዲያ ዝም ብንልም ወንጀለኞች ሆነናን። ዝምታው ይሰበር በአንድነት የጉዳዩ ተጠቂ ነን እንበል! ኢትዮጵያ የሁላችንም ነች! ኢትዮጵያ የዚህ የዚያ ብሄር አይደለችም የሁላችንም ነች። ከጠባብ የብሄር ጎጠኞች ኢትዮጵያን እንታደጋት!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!
              

     

                  The ESAT Society: Ethiopian Satellite Television

Ethiopian Satellite Television (ESAT logo)Established on April 24, 2010 “to promote free press, democracy, respect for human rights and the rule of law in Ethiopia”, the Ethiopian Satellite Television Service (ESAT) becomes one of the most trusted and reliable broadcast media. ESAT has its main studio in Amsterdam and branch studios in Washington D.C. and London. Its radio and television programmes cover nearly all socio-economic, cultural and political issues and topics. The major audience is the Ethiopian majority who happens to suffer from lack of credible and non-partisan media. In just nearly three years and despite serious interference by the Ethiopian government, ESAT is successfully creating a society of its own. A society who longs for freedom of all kinds, rule of law, and democratic governance in Ethiopia.

In this paper, I first try to highlight the various roles ESAT is playing to meet its objectives. Well, one could argue that its role is one and one- to be an independent and credible voice to the voiceless. This is obvious but my focus is on the specific roles ESAT is playing in its effort to reach its audience. Through such an exposition, it is possible to better meter to what extent ESAT services are being delivered to a variety of people. In the second part of the paper, I raise some important issues and challenges that should attract ESAT’s and the audience’s attention for a much higher impact. The issues and challenges may relate to the services and future engagements.
My motivation to write this paper is related to ESAT fund raising events taking place in several European cities. Europe is being astounded by the famous and all-times trusted human rights activist, Tamagn Beyene. Discussions among friends and families in Europe are about ESAT and Tamagn. My discussion with a friend of mine stimulated the write up of this paper. Generally, the paper has that purpose of 1) commending ESAT for its services so far, and 2) suggesting other ways of scaling up and sustaining its services.

ESAT Roles

The following roles presumably characterize ESAT as an independent voice for the voiceless. Mainly because of the multitude of roles it plays, ESAT managed to stand stronger and taller than before. Keeping up and expanding those roles is crucial for its future existence.

Distance breacher

ESAT is a particularly useful asset for the Ethiopian Diaspora who is living thousands of miles away from home. Living and working abroad for an indefinite time is a challenge for the many. They feel detached from their country and feel unable to contribute. Even government communicators argue that the Diaspora play an alien politics because they have no first-hand touch with reality in Ethiopia. But now and thanks to ESAT, we feel as if we reside in Ethiopia. We hear and see Ethiopians from North to South, West to East part of the country talking on ESAT. We feel as if we are brought closer to Ethiopia. That is because distance is breached by ESAT.

Reliable friend

Due to work and other obligations, Ethiopian Diaspora seem to have limited time to spend in a social milieu. And in several cities, even husband and wife do not have much time to spend together. That may create a sense of loneliness and detachment. Thanks to advances in smartphone and tablet technologies, ESAT demonstratively plays a role of a reliable and credible friend. At work, on our way, at home and elsewhere, ESAT is with us. That creates a sense of up-to-datedness, community, and freedom.

Bridge maker

People from the Haile Selassie generation, the Mengistu HaileMariam times, and the ‘new’ generation co-exist in 21st Century Ethiopia. These three generations are significantly different in a whole array of fronts: on views of society, government, democracy, development and so forth. The ‘old’ generation did not have forum for meaningful discussion with the new generation. Worst is that there is a misunderstanding between the generations when it comes to Ethiopia’s ‘yesterday’ politics. Because of ESAT, the new generation get that excellent chance of talking and listening to several of the most influential personalities of the old generation. I could argue that ESAT is surely creating a bridge between the ‘that generation’ and ‘this generation’.

Think tank

Professionals from the old and new generations are getting interviewed on ESAT. Our knowledge of key social issues such as economics, education, politics, technology, military, and so forth is improving. All these are definitely crucial for public policy making. Although government policy makers and planners do not openly thank ESAT, they could attend to its services and hence they could get important lessons to draw on. Even if they do not do that, the knowledge being created will be seminal for people interested to study Ethiopia. But for now, our understanding of key issues is self-fulfilling and empowering, thanks to ESAT. In a way, ESAT could also be considered as a think tank that could better inform individuals and public policy makers and planners.

Common platform

ESAT aims to be the voice of the voiceless. The question is: who are the voiceless? Are the silent Ethiopian majority the voiceless? Are opposition politicians and parties the voiceless? Are the ‘independent’ the voiceless? Yes, all these could be considered the voiceless because they are denied of their natural and constitutional rights to freely assemble, talk and oppose. Talking truth is these days tantamount to being a terrorist. Trying to hold the governing party accountable for what it is doing is considered an effort to disrupt peace and retard development initiatives. These are the real voiceless.
Surprisingly enough, even people from the governing party are using ESAT as their voice. Mister Sebhat Nega, perhaps the most disgruntled and mannerless politician Ethiopia ever saw, is gashing out his grievances and frustrations through ESAT. Other politicians from the governing party, even Bereket Simon who persecutes journalists and who works day and night to block ESAT, are constantly invited to talk to millions of Ethiopians through the common platform- ESAT. This role is edifying and should be sustained.

The Invincible

EPRDF has that so far proven to be effective strategy of weeding out journalists, human right defenders, politicians, and academics from Ethiopia. The party puts immense pressure to make sure such people leave for foreign lands. The assumption is that once migrated, they would distance themselves from political struggle because they would spend their entire time and resources simply to cope up with the new demands of life abroad. And that strategy worked well for decades until ESAT decided to push it to the limit. In one way or another persecuted journalists created that front and started to ‘fight’ back. This sends shockwaves to Government Communications Officer Bereket Simon and to the entire EPRDF structure. They managed to block ESAT services for some time. But ESAT appeared the invincible.
This is a great lesson to all Ethiopian professionals: the spirit of invincibility even if they are thousands of miles away from home. I wish medical doctors, academics, lawyers, engineers and other professionals in the Diaspora create genuine associations and then to start contributing to ensure freedom, democracy, and human rights. Issues and

Challenges

Even for a better service, ESAT needs to consider some issues mentioned below. I am not concluding that ESAT board and/or the management are not aware of these as I do not have information on that. I just would like to express the concerns several people are entertaining in one way or the other. The assumption is that if ESAT adequately and timely deals with the following issues and challenges, it will create much more confidence in its audience. That is in the end seminal to garner sustained public support sufficient enough to let ESAT stay on air.

Improved transparency

ESAT website maintains useful information about its policy and general integrity. This is useful but a lot more should be said about the organization itself. Who are members of ESAT Board, for instance? And who are the management? And who is the editor-in-chief? I do not think that ESAT wants to keep the identity of staff and board members confidential. They are at the forefront of the struggle for freedom and hence keeping the identity of those who are on the frontline makes little sense.

Eye on the future

Mainly because of the gigantic nature of our daily political problems, ESAT seems to devote much of the effort on present-day Ethiopia. This is extremely useful as it will help us to make informed decisions at individual and group/collective levels. While focusing on the present, it is extremely necessary to make future-oriented analyses and predictions as well. For instance, what kind of governance is best for Ethiopia? What should be Ethiopia’s future positioning when it comes to foreign policy? What social, economic, and political issues might be strangling Ethiopia in the future? How could we sort of maneuver and make collective decisions to survive? These and related issues could be addressed through expert panels, formal studies, and simulations.

Elitism

For issues related to credibility, impact, and of course media tradition, it seems better to invite experts and the elderly to make presentations or interviews. That is what ESAT has been doing. We have had that excellent chance of learning from professionals from diverse backgrounds. As a voice of the voiceless, it may be interesting and useful to interview ordinary citizens, too. Allowing the audience to leave short messages would not be sufficient to ensure participatory efforts. It is thus vital to interview youngsters, kids, and others on whole diverse issues. This way, ESAT could better understand people perceptions and views, which could then be used as stepping stones for further nuanced discussions.

Ethiopians only

So far, ESAT interviewed Ethiopians only (I mean Ethiopian by birth) with few exceptions. This is not a problem itself. But we could also learn from the experiences of other people. If resources allow, it would be great to interview Eritreans, Somalis, other Africans and other people from the rest of the world. Doing that would be educative and would help to popularize ESAT. It is also useful to galvanize the rest of the world to make commitments to human rights and rule of law in Ethiopia and elsewhere in the world.


                     

                                                     
   

    

“ተቃዋሚዎች ምርጫውን ከሚያሸንፉ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ---” - ሁጐ ቻቬዝ ቬኔዝዌላ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ አምባገነን ባለስልጣናት


“ተቃዋሚዎች ምርጫውን ከሚያሸንፉ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ---” - ሁጐ ቻቬዝ ቬኔዝዌላ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ አምባገነን ባለስልጣናት

“ ኧረ መልሱን ስጪኝ ዝምታው ምንድነው ቅድምም አሁንም የመረጥኩ አንቺን ነው” ባለፈው ማክሰኞ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የቬኔዝዌላ ፕሬዚዳንት ሁጎ ቻቬዝ፤ በጣም ዝነኛ ነበሩ - ሰውን በመዘርጠጥና በመዝለፍ፡፡ በቀዳሚነት መዝለፍና መዘርጠጥ የሚቀናቸው የሥልጣን ተፎካካሪዎቻቸውን ተቃዋሚዎችን ነበር፡፡ በመቀጠል ደግሞ የአሜሪካን ፕሬዚዳንትና ካፒታሊዝምን እንደጉድ ሲዘረጥጡና ሲያብጠለጥሉ ኖረዋል (የነዳጅ ሃብታቸው በሰጣቸው የልብ ልብ!) ሁጐ ቻቬዝ እ.ኤ.አ በ1999 ዓ.ም እጩ ፕሬዚዳንት ሳሉ አንዳንድ የተጠራጠሯቸው ወገኖች አጓጉል ጥያቄዎች አቅርበውላቸው ነበር፡፡ (ያውም እኮ በሥልጣን ዙሪያ!) “በአምስት ዓመት ውስጥ ሥልጣን ያስረክባሉ?” ተባሉ (አያችሁ ሠይጣን ሲፈትናቸው!) እሳቸውስ ምናቸው ሞኝ ነው! “እንዴታ! እንደውም ቀደም ብዬ ለማስረከብ ፈቃደኛ ነኝ” አሉና ቂብ አሉ - የሥልጣን መንበሩ ላይ፡፡

ከዚያማ ማን ወንድ ይምጣ - ከሥልጣን የሚያወርዳቸው፡፡ አምስት ዓመት ሳይሞላኝ እወርዳለሁ ያሉት ቻቬስ፤እንደሌሎቹ አምባገነን ባልንጀሮቻቸው ህገመንግስት እየሰረዙና እየደለዙ ቬኔዝዌላን ለ14 ዓመታት እንዳሻቸው ፈነጩባት (ፈነዱባት ይሻላል!) ፕሬዚዳንቱ ምርጫ በመጣ ቁጥር ተቀናቃኞቻቸውን ሙልጭ አድርገው በመስደብና በማንጓጠጥ ይታወቃሉ፡ (እንደኢህአዴግ “መጡም ቀሩም አይጠቅሙም አይጎዱም” ዓይነት እንዳይመስላችሁ!) አምባገነንነት ላይ የነዳጅ ዶላር ሲጨመርበት ምን እንደሚከሰት አስቡት! የማታ ማታ ግን ለሁለት ዓመት ያህል ከካንሰራቸው ጋር ሲታገሉ ቆይተው ህይወታቸው አለፈ - ከሥልጣን ሱሳቸውም ተገላገሉ፡፡ ሶሻሊዝም አቀንቃኝ የነበሩት የዓለማችን አወዛጋቢው ፕሬዚዳንት ቻቬዝ ስለካፒታሊዝም ሲናገሩ፤ “አዲስና የተሻለ ዓለም ለመገንባት ትክክለኛው መንገድ ካፒታሊዝም አይደለም ፤ ካፒታሊዝም በቀጥታ የሚወስደን ወደ ገሃነም ነው” ብለው ነበር፡፡
ለመሆኑ አሁን እሳቸው ያሉት የት ነው? ገነት ነው ገሃነም? (ገነትም ሆነ ገሃነም ያቺ የሚወዷት ሥልጣን ምድር ቀርታለች!) ስለቀድሞው የቬኔዝዌላ ፕሬዚዳንት እቺን ታህል ካወጋን ለጊዜው ይበቃናል (ለአምባገነን ብዙ የአየር ሰዓት ሰጠሁ እንዴ?) አሁን ደግሞ ወደራሳችን ገበና እንዝለቅ (አዲስ የኢቴቪ ድራማ እንዳይመስላችሁ!) ወደ ፖለቲካ ገበናችን ማለቴ ነው፡፡ እኔ የምላችሁ… በፓርቲዎች የአየር ሰዓት ድልድል ዙሪያ ሰሞኑን የተደረገውን ማሻሻያ እንዴት አያችሁት? መቼም ህውሀት/ወያኔ ቶሎ መስማት አይሆንለትም አይደል! (ጆሮው ስለሚኮራ እኮ ነው!) ዛሬ ያደረጋትን ማሻሻያ ፤ ባለፈው ምርጫ ወይም ከዚያ በፊት በነበረው ምርጫ ቢያደርገው እኮ ስንት ዲሞክራሲ ባዳነ ነበር! (“ለዲሞክራሲው ሲባል ነው” የሚል ነገር ሰምቼ እኮ ነው) በነገራችሁ ላይ ኢህአዴግ “መብቴን ወይም ነፃነቴን ውለዳት” ሲሉት አይወድም ፤ እልህ ውስጥ ይገባል፡፡
ክፋቱ ደግሞ ተቃዋሚዎቹም ከሱ ስለማይሻሉ በጥበብና በብልሃት አይዙትም (እልህን በእልህ ባይ ናቸው!) በነገራችሁ ላይ የሚያዝያውን ምርጫ አስመልክቶ ለፓርቲዎች የተደለደለው የአየር ሰዓት 9ሚ.ብር የሚገመት ነው ተብሏል (ለዲሞክራሲ 90 ሚሊዮንም አይቆጭም!) በኢቴቪ መግለጫ ሲሰጡ የሰማኋቸው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሃላፊ (“ፓርቲዎችን አላበላልጥም ፤ እንደ ልጆቼ ነው የማያቸው” ያሉትን ፕሮፌሰር ማለቴ ነው!) የአየር ሰዓት ድልድሉ ተቃዋሚዎችን በሚጠቅም መልኩ የተሻሻለው “ለዲሞክራሲው ሲባል ነው” ብለዋል (ለምንም ይሁን …ብቻ እንኳን ተሻሻለ!) አንድ ጥያቄ አለኝ ---- ለምንድነው የአየር ሰዓት ድልድሉ ለአሁኑ ምርጫ ብቻ ነው የተባለው? (“የአየር ሰዓትም” ከእነዎርልድ ባንክ በብድር እንጠይቅ ማለት ነው?) ቀደም ሲል የአየር ሰዓት ድልድሉ ፓርቲዎች በም/ቤት ባላቸው መቀመጫ ብዛት የሚከናወን እንደነበር ያስታወሱት ፕ/ር መርጊያ፤ “አሁንም ማቲማቲካሊ እንጂ ፕሪንሲፕሉ አልተቀየረም” ሲሉ አስረድተዋል፡፡ (ነገር እንዳይመጣ ሰግተው እኮ ነው!) ከድፍረት አይቆጠርብኝና … አንዳንድ “ለዲሞክራሲው ሲባል” መሻሻል ወይም መለወጥ ያለባቸውን ነገሮች ብጠቁምስ? (በእልህ ሳይሆን በፒስ!) አሁን ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ኢህአዴግ ምን አለ? “መድረክ” የምርጫ ሥነምግባር ደንቡን ካልፈረመ አላናግረውም ብሎ ይኸው ዝም ጭጭ ተባብለው የለ - በአገር አማን!! እኔ የምለው ግን--- ደግሞ ለመነጋገር ምን ፊርማ ያስፈልጋል? (የሚኮራረፉ ፓርቲዎች ያላት ብቸኛ አገር ኢትዮጵያ ሳትሆን አትቀርም!) እናላችሁ --- ኢህአዴግ “እንደራደር” እያሉ ከሚወተውቱት ተቃዋሚዎች ጋር እሺ ብሎ ቢደራደር አሸነፈ እንጂ አልተሸነፈም (ፈርሙ አትፈርሙ የሚለውን ንትርኩን ወዲያ ትቶ!) ለምን መሰላችሁ ---
- “ለዲሞክራሲው ሲባል” ነው! ከ“ዝነኛው” የ97 ምርጫ ማግስት ጀምሮ ጠበበ እንጂ ሰፋ ተብሎ የማይታወቀው የፖለቲካ ምህዳር ለምን በደንብ አይሰፋም? (ለዲሞክራሲው ሲባል“ ማለቴ ነው) ተቃዋሚዎች የፓርቲ ልሳናቸውን የሚያሳትሙበት ማተምያ ቤት፣ ስብሰባ የሚያካሂዱበት አዳራሽ ወዘተ--- ለምን አይመቻችላቸውም? (ያው “ለዲሞክራሲው ሲባል”!) የመጨረሻ ጥያቄ አለኝ ---- በ21 ዓመት የኢህአዴግ የሥልጣን ዘመን በጉጉት ጠብቀን ጠብቀን “ሲያምራችሁ ይቅር” የተባልነው አንድ ነገር አለ፡፡ የግል የቴሌቪዥን ጣቢያ! እናም “ለዲሞክራሲው ሲባል” የግል የቴሌቪዥን ጣቢያ ይፈቀድልን ዘንድ ህገመንግስታዊ መብታችንን እንጠይቃለን (በእልህ ሳይሆን በፒስ!) እስከዚያው ግን ለ“ልማታዊው ፓርቲያችን” ለኢህአዴግ የተፈራ ካሳን ዜማ እንመርጥለታለን፡፡
ኧረ መልሱን ስጪኝ ዝምታው ምንድነው ቅድምም አሁንም የመረጥኩ አንቺን ነው--- የሚለውን፡፡ እኔ የምላችሁ… ኢህአዴግ በቅርቡ በባህርዳር ለሚያካሂደው 9ኛው ጉባኤ 15 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ከውጭ አገራት እንደጋበዘ ሰማችሁ አይደል? (የአገር ቤት ፓርቲን ትቶ ከውጭ “መቀላወጥ” ምን ይሉታል?) በጣም እኮ ነው የሚገርመው ---- ኢህአዴግ ከአገር ውስጥ አንድ ፓርቲ እንኳን ሳይጋብዝ አስራምናምን ከውጭ? (የፓርቲ ጉባኤ ድንኳን ሰበራ እንዳይጀመር ሰጋሁ!) ቆይ ግን--- ይሄ ጉደኛ ፓርቲ እነዚህን ሁሉ የፓርቲ ባልንጀራዎች መቼ ነው የተዋወቃቸው? እዚህ ከአንድ ተቃዋሚ ጋር በተጣላ ቁጥር ውጭ ካለ አንድ ፓርቲ ጋር ባልንጀርነት ሲመሰርት ነበር ማለት ነው? የኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሴኮ ቱሬ (የስማቸውን ፍቺ ባውቀው ደስ ይለኝ ነበር) ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፤ የኢህአዴግ ዘጠነኛ ጉባኤ ፓን አፍሪካኒዝምን ያንፀባርቃል ብለዋል፡፡
(በአገር ውስጥ ባለው የፓርቲዎች ግንኙነት አኩሪ ታሪክ ባይኖረውም ማለት ነው!) አንድ ነገር ግን መዘንጋት የለበትም፡፡ ምን መሰላችሁ--- ለሌሎች ሃሳባችንንና መስመራችንን ስናጋራ ልዩ ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡ ሁሉ ነገራችንን ዘርግፈን መስጠት የለብንም፡፡ ለምን መሰላችሁ --- አንዳንዴ እንጠቅማለን ብለን ልንጎዳ እንችላለን፡፡ አያችሁ ---
ኢህአዴግ ለአፍሪካውያን የሚያጋራው በጎ በጎ ነገሮች እንዳሉት ቢናገርም ሁሉንም ፈጽሞ ማጋራት የሌለበት አሉታዊ ነገሮችም እንዳሉት ግምት ውስጥ ማስገባት አለበት!! እስቲ አስቡት…የፓርቲውን የ“ምስጢራዊነት” ባህል ለሌሎች አፍሪካውያን ቢያጋራ ምን ዓይነት ችግር ላይ እንደሚወድቁ! (ለራሱም እኮ አልጠቀመውም) “እኔ ብቻ ነኝ የአገር መድሃኒት” የሚለውንም ጎጂ ባህሉን ለአፍሪካ ወንድሞች ማጋራት የለበትም (ትርፉ ዕዳ ነዋ!) የፍረጃ ልምዱንም (ኪራይ ሰብሳቢ፣ የሻቢያ ተላላኪዎች፣ ጥገኞች…ወዘተ) አጋራለሁ ብሎ እንዳያስብ እንመክረዋለን (እንዴ ማፈሪያ ይሆናላ!) ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢህአዴግን ሲበዛ ባተሌ መሆን ለአንድ ሁነኛ ባልንጀራዬ ሳወያየው ምን እንዳለኝ ታውቃላችሁ… “ኢህአዴግ የተባለ ሁሉ (አመራር፣ ካድሬ፣ አባል ወዘተ…) ከምርጫው በኋላ ቫኬሽን ይወጣል” “ኧረ ይገባቸዋል…ግን ለምን ያህል ጊዜ ነው?” ጠየቅሁት፡፡ “እስከቀጣዩ ምርጫ!” “እስከ ቀጣዩ ምርጫ? እስከ 2007 ማለትህ ነው?” “አግኝተኸኛል … ያኔ ምርጫ ሲቃረብ ደግሞ ስብሰባ፣ ውይይት፣ ብሶት መስማት … የኮንዶሚኒየም እጣ ማውጣት፣ የልማት ዲስኩር … መቀወጥ ይጀምራሉ … ምርጫው ሲጠናቀቅ እንደገና ቫኬሽን …” “ቆይ እነሱ ቫኬሽን ሲወጡ ማነው የሚመራው … ማለቴ … የሚያስተዳድረው?” “እነሱው! ካሉበት ሆነው በሞባይል ያስተዳድሩናል … በሞባይል ያዛሉ … በሞባይል ቅሬታ ይሰማሉ … በሞባይል ደንብና መመሪያ ያወጣሉ … ቀላል ነው … ለምደውታል” “ምኑን?” “ቫኬሽን ላይ ሆኖ አገር መምራቱን!” ትንሽ ቆዘምኩ፡፡
ትንሽ አሰብኩ፡፡ አሰላሰልኩ፡፡ በኋላ እንዲህ አልኩ - ለራሴ፡፡ “እነሱ ቫኬሽን ሲወጡ እንኳን ለምን ለተቃዋሚዎች አይሰጧቸውም?” (አገር መምራቱን ማለቴ ነው!) እኔ የምለው ግን ---- ኢህአዴግ ወተት በየቤታችን በቧንቧ ያስገባልናል ብለን ስንት ስንኩራራ እንዲህ ያሳፍረን! (ውሃውም ጠፋ እኮ!) አንድ ለልጃቸው ሠርግ ደፋ ቀና ሲሉ የነበሩ እናት አንዴ መብራት፣ ሌላ ጊዜ ውሃ እየጠፋ ሲቸገሩ ምን አሉ መሰላችሁ? “ይሄንን ጠላ ጅቡቲ ሄጄ ካልጠመቅሁት ጠላም አይሆን!” አሁን ደግሞ ስለ ቻቬዝ ትንሽ እናውጋ፡፡ አንዴ ስለአገራቸው ተቃዋሚዎች ምን አሉ መሰላችሁ? “ተቃዋሚዎች አስቂኝ ስለሆኑ ማታ ማታ ልጆቻችንን ያዝናኑልናል” (እንደኛ አገር ተቃዋሚ ከሆኑ በጨጓራ በሽታ ይቃጠላሉ!) እ.ኤ.አ በ2002 ዓ.ም ለአጭር ሰዓታት የዘለቀ ኩዴታ ተሞክሮባቸው የነበሩት ቻቬዝ፤ የሞት ሞታቸውን እንዲህ የሚል መግለጫ ሰጥተው ነበር- “በእስረኝነት የተያዝኩ ፕሬዚዳንት ነኝ እንጂ ሥልጣን አለቀቅሁም” (ይሞታል እንዴ!) እ.ኤ.አ በ2012 ለትንሳኤ በዓል በተሰበሰበ ምዕመን ፊት እያለቀሱ የታዩት ቻቬዝ፤ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው “ኢየሱስ፤ መስቀልህን አምጣ ልሸከም … ገላዬ እንዲደማም የእሾህ አክሊልህን ስጠኝ … ግን መኖር እፈልጋለሁ … ለዚህ አገርና ህዝብ ብዙ የምሰራው አለኝ … ሩጫዬን ገና አልጨረስኩምና እንዳትወስደኝ” (ሥልጣን አልበቃኝም ቢሉ ይሻላቸው ነበር) መቼም ቻቬዝ ---እንደ አሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆርጅ ቡሽ የሚጠሉት ሰው አልነበረም ፤ እናም በተደጋጋሚ ሰድበዋቸዋል፡፡ አንዴ ራሳቸው በሚያዘጋጁት የቲቪ ቶክ ሾው ላይ “የአልኮል ሱሰኛ፣ ሰካራም፣ ውሸታም፣ የነቀዝክ … አዕምሮህ የተነካ በሽተኛ!” ሲሉ ሞልጨዋቸዋል፡፡ የእንግሊዝ ጠ/ሚኒስትር የነበሩት ቶኒ ብሌርም ከመሞለጭ አልዳኑም “የኢምፔሪያሊዝም ታጋች ነህ … ገሃነም ግባ!” ብለዋቸዋል፡፡ ቻቬዝ የካፒታሊስት አገራት መሪዎች ቀንደኛ ጠላት የነበሩትን ያህል የሶሻሊስቶቹ ወዳጅ እንደነበሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2007 ዓ.ም ኩባ ሄደው የነበሩት ሁጐ ቻቬዝ፤ፊደል ካስትሮን ሲያደንቁ “በዚህች አህጉር የተካሄዱ አብዮቶች አባት ነህ፤ የኛም አባት አንተ ነህ” ብለዋቸዋል፡፡
ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ከካንሰር ህመማቸው ጋር ክፉኛ እየታገሉ ለፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የተወዳደሩት ቻቬዝ፤ ተቃዋሚዎቻቸውን ተስፋ ለማስቆረጥ ጉልበት አላጡም ነበር፡፡ (ኢህአዴግም አንዳንዴ ይነሳበታል እኮ!) ለማንኛውም እሳቸው ያሉት እንዲህ ነበር “ተቃዋሚዎች ምርጫውን ከሚያሸንፉ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይሻላል” ይሄ አባባል ለኛም ይሠራል እንዴ? (ቢያንስ በአሁኑ ምርጫ!) ሥልጣን የሌለበት አገር የሄዱት ቻቬዝ (ቢኖርም የሚሰጣቸው የለም!) ስለ ሶሻሊዝምና ካፒታሊዝም በተናገሩት አባባል የዛሬ ፖለቲካዊ ወጋችንን እንቋጭ - “ካፒታሊዝም የሰይጣንና የብዝበዛ ሥርዓት ነው - የመጀመርያው ሶሻሊስት ነው ብዬ በማስበው በኢየሱስ ክርስቶስ ዓይን ነገሮችን ማየት የምትሹ ከሆነ እውነተኛ ህብረተሰብ መፍጠር የሚችለው ሶሻሊዝም ብቻ ነው” ምንም እንኳን ቻቬዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እቺን ዓለም ቢሰናበቱም በተለይ በካፒታሊዝምና በአሜሪካ መሪዎች ላይ በተናገሯቸው የዘለፋ ቃላት መታወሳቸው አይቀርም (ባያኮራም!)
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!
ከሰብኣዊ

እኔ የምላችሁ… ኢህአዴግ በቅርቡ በባህርዳር ለሚያካሂደው 9ኛው ጉባኤ 15 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ከውጭ አገራት እንደጋበዘ ሰማችሁ አይደል? (የአገር ቤት ፓርቲን ትቶ ከውጭ “መቀላወጥ” ምን ይሉታል?) በጣም እኮ ነው የሚገርመው ---- ኢህአዴግ ከአገር ውስጥ አንድ ፓርቲ እንኳን ሳይጋብዝ አስራምናምን ከውጭ? (የፓርቲ ጉባኤ ድንኳን ሰበራ እንዳይጀመር ሰጋሁ!) ቆይ ግን--- ይሄ ጉደኛ ፓርቲ እነዚህን ሁሉ የፓርቲ ባልንጀራዎች መቼ ነው የተዋወቃቸው? እዚህ ከአንድ ተቃዋሚ ጋር በተጣላ ቁጥር ውጭ ካለ አንድ ፓርቲ ጋር ባልንጀርነት ሲመሰርት ነበር ማለት ነው? የኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሴኮ ቱሬ (የስማቸውን ፍቺ ባውቀው ደስ ይለኝ ነበር) ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፤ የኢህአዴግ ዘጠነኛ ጉባኤ ፓን አፍሪካኒዝምን ያንፀባርቃል ብለዋል፡፡
(በአገር ውስጥ ባለው የፓርቲዎች ግንኙነት አኩሪ ታሪክ ባይኖረውም ማለት ነው!) አንድ ነገር ግን መዘንጋት የለበትም፡፡ ምን መሰላችሁ--- ለሌሎች ሃሳባችንንና መስመራችንን ስናጋራ ልዩ ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡ ሁሉ ነገራችንን ዘርግፈን መስጠት የለብንም፡፡ ለምን መሰላችሁ --- አንዳንዴ እንጠቅማለን ብለን ልንጎዳ እንችላለን፡፡ አያችሁ ---ኢህአዴግ ለአፍሪካውያን የሚያጋራው በጎ በጎ ነገሮች እንዳሉት ቢናገርምሁሉ ፈጽሞ ማጋራት የሌለበት አሉታዊ ነገሮችም እንዳሉት ግምት ውስጥ ማስገባት አለበት!! እስቲ አስቡት…የፓርቲውን የ“ምስጢራዊነት” ባህል ለሌሎች አፍሪካውያን ቢያጋራ ምን ዓይነት ችግር ላይ እንደሚወድቁ! (ለራሱም እኮ አልጠቀመውም) “እኔ ብቻ ነኝ የአገር መድሃኒት” የሚለውንም ጎጂ ባህሉን ለአፍሪካ ወንድሞች ማጋራት የለበትም (ትርፉ ዕዳ ነዋ!) የፍረጃ ልምዱንም (ኪራይ ሰብሳቢ፣ የሻቢያ ተላላኪዎች፣ ጥገኞች…ወዘተ) አጋራለሁ ብሎ እንዳያስብ እንመክረዋለን (እንዴ ማፈሪያ ይሆናላ!) ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢህአዴግን ሲበዛ ባተሌ መሆን ለአንድ ሁነኛ ባልንጀራዬ ሳወያየው ምን እንዳለኝ ታውቃላችሁ… “ኢህአዴግ የተባለ ሁሉ (አመራር፣ ካድሬ፣ አባል ወዘተ…) ከምርጫው በኋላ ቫኬሽን ይወጣል” “ኧረ ይገባቸዋል…ግን ለምን ያህል ጊዜ ነው?” ጠየቅሁት፡፡ “እስከቀጣዩ ምርጫ!” “እስከ ቀጣዩ ምርጫ? እስከ 2007 ማለትህ ነው?” “አግኝተኸኛል … ያኔ ምርጫ ሲቃረብ ደግሞ ስብሰባ፣ ውይይት፣ ብሶት መስማት … የኮንዶሚኒየም እጣ ማውጣት፣ የልማት ዲስኩር … መቀወጥ ይጀምራሉ … ምርጫው ሲጠናቀቅ እንደገና ቫኬሽን …” “ቆይ እነሱ ቫኬሽን ሲወጡ ማነው የሚመራው … ማለቴ … የሚያስተዳድረው?” “እነሱው! ካሉበት ሆነው በሞባይል ያስተዳድሩናል … በሞባይል ያዛሉ … በሞባይል ቅሬታ ይሰማሉ … በሞባይል ደንብና መመሪያ ያወጣሉ … ቀላል ነው … ለምደውታል” “ምኑን?” “ቫኬሽን ላይ ሆኖ አገር መምራቱን!” ትንሽ ቆዘምኩ፡፡

Saturday, March 9, 2013

የህወሓት ስረወመንግስት በኢሕኣዴግ ጡዘት


“የህወሃት የበላይነት በእኩልነት”

ተጠፍጥፈው በወያኔ የተሰሩት የኢሕኣዴግ አባል ድርጅቶት እስከዛሬ እንዳልተዋሃዱ የሚታወቅ ነው:: እንዚህ ድርጅቶች ባለፉት 20 አመታት ውስጥ ያልተዋሃዱበት እና በአንድtplf rotten appleፓርቲ እና ግለሰብ ስር እየተሽከረከሩ የኖሩበት ሁኔታ በበረሃው የመሃላ ፖለቲካ አለምብሰላቸው ወደ ሕወሓት ስረወመንግስት ውሳኔ ሰጪነት ሳያሸጋግራቸው የፖለቲካ ባሮች እንደሆኑ አሉ::ርእዮት አለሙ እጅግ ወደ ኋላ የቀረ እና የአስተሳሰብ ጥልቀቶች አለመኖር ፓርታዊ ዲሞክራሲን ማእከል አለማድረጋቸው የውህደት ምህዳሩ እንዲደፈን እና ብሔር ተኮር የውህደት አደረጃጀት ወደ ሃገራዊ ፓርቲነት እንዳይለወጡ ለውህደቱ ዚግዛግ እደምታ አስከትሎበታል::ይህ ደሞ ሕወሓት የበላይነቱን እዳያጣ እና ስረወመንግስት እንዳይደረመስ ከመፍራት በመጣ የተቀነባበረ የፖለቲካ ሴራ ነው::
በባህር ዳር ይካሄዳል ተብሎ እየተጠበቀ ያለው የኢሕኣዴግ ጉባኤ እጅግ በተጠንቀቅ እየተጠበቀ ሲሆን ፓርቲዎች ላለፉት አመታት እየተደረገባቸው ያለውን የፖለቲካ ጭቆና በተመለከተ ያፈነዱታል ተብሎ ተሰግቷል:: ለዚህን በአሁን ሰአት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል:: የግንባሩ አባል ድርጅቶች በሕወሃት ላይ ያላቸውን ጥላቻ ያንጸባርቁበታል ድርጅታዊ መብታቸን በፋት ይጠይቁበታል የተባለለት ይህ ጉባየ ሌሎች ችግሮችንም እንደሚወልድ እየተነገረለት ነው::እነዚሁ አባል ድርጅቶች “የህወሃት የበላይነት በእኩልነት” የሚል አዲስ አስተሳሰባቸውን ይዘው ስለሚቀላቀሉ ፍራቻውን ለማስወገድ ተሳታፊ አባላት ሲመረጡ ጥንቃቄ እንዲወሰድ ስራዎች ተሰርተዋል::በግንባሩ ላይ የለውጥ ተጸኖ ያሳድራሉ የተባሉ ተሳታፊዎች ወደ ባህር ዳር እንዳይዘልቁ በመደረጉ ችግሮች እንዳመረቀዙ ነው ያሉት::

ራሳቸውን ስልጣን ላይ ለማቆየት የተለያዩ መርሆዎችን የሚከተሉት ወያኔዎች በለውጥ ጎዳና የሄዳሉ ማለት ዘበት ነው::መርሆዎቻቸው የህብረተሰቡን መብቶች እና የሃገሪቱን የምጣኔሃብት እድገቶች ከማኮላሸት ዉጪ ምንም ፋይዳ የላቸውም::በአብዮታዊ ዲሞክራሲ የተመረዙ የፖለቲካ እና የምጣኔሃብት አጀንዳዎች ያሉት ኢህኣዴግ የዴሞክራሲ ተፈጥሮ ሰላለለው ስልጣኑ በእጁ ስላለ ባለስልጣኖቹ የህዝብን መብትና ንብረት ለጥቅማቸው አውለውታል:: እጅግ በሚደንቅ ሁኔታ ነጋዴ ያልሆኑ ኢትዮጵያውያን ባለስልጣኖች Bank of Malaysia በከፈቱት አካውንት ከፍተኛ የዶላሮች ክምችት እንዳላቸው መረጃዎች ጠቆሙ:: በሃገር ውስጥ ያሉ የምእራባውያን ዲፕሎማቶች እይታዎች እንደሚያሳዩት የኢትዮጵያውያን ባለስልጣናት ራሳቸው በፈጠሩት በራሳቸው እና በቤተሰባቸው ስም የተለያዩ አካውንቶች ውስጥ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን እንዳስቀመጡ በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ የረድኤት ድርጅት ዲፕሎማቶቹ ያደረሱት መረጃ አመላክቷል::እንዲሁም በኳታር;በሲንጋፖር;በታይዋን;በቱርክ.. የተለያዩ የባንክ አካውንቶች ያሏቸው ሲሆን በምእራቡ አለም እምብዛም ባንኮችን አይጠቀሙም::
የመድበለ ፓርቲን በመርህ ደረጃ ብቻ የሚቀበለው ወያኔ ለመተግበር ስለሚከብደው ካድሬዎቹ በራሳቸው ድንጋጠ ውስጥ የከተታቸው ሲሆን ታማኝነቱን አጉድሎታል:;በምላሱ ብቻ የሚናገራቸው የዲሞክራሲ መርሆዎች ከካድሬዎቹ የፖለቲካ ማንነት ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል::
ባለፉት 20 አመታቶች ውስጥ ኢትዮጵያውያን እምነት እንዳጡበት ደጋግመው ያሳዩ ወያኔ አሁንም አስተማማኝ የተባለ መንገድን ለመጥረግ ዝግጁ ባለመሆኑ እና ጀሌዎቹም ባንድ ወጥ ውሳኔ አሰጣት ያልሰለጠኑ የፖለቲካ ታማኞች በመሆናቸው በቀታይነት ከወያኔ ምንም እንደማይጠበቅ የወቁ ብዙሃን ህዝቦች ይህን ስረወመንግስት ለመናድ በስፋት እየዘመቱ ይገኛል:;
በፍትህ ስርኣቱ ታማኝነቱ ተጠሪነቱ ለመንግስት መሆኑ አሁንም ዋና እና አነጋጋሪ ይርሆነ ጉዳይ ሲሆን ወያኔ ካለፉት መንግስታት ምንም አይነት የፍርድ ቤቶችን አሰራር በተመለከት ትምህርት አላመቅሰሙ ሊያስጠይቀው የሚገባ ጉዳይ ነው የደርግን መንግስት እንኳን ብንወስድ ቀይ ሽብርን የፈጸመው ከፍርድ ብት ውጪ እንደነበር እና ከዛም በሁዋላ በነበሩ ጊዜያት ታስረው የነበሩ ማናቸውም ሰዎች ከደርግ ጣልቃ ገብነት ውጭ ፍርድ ቤቶች የራሳቸውን ውሳኔ ይሰጡ እንደነበር የሚያውቁ ይመሰክራሉ::በአሁኑ ሰአት ግን እያንዳንዱ ህብረተሰብ በፍትህ ተቋማት ላይ ትልልልልቅ ጥያቄዎች እያነሳ ነው::
የወያኔ መንግስት በበረሃ ታግሎ የመጡት እና የድል አጥቢያ አርበኞት የእርስ በእርስ አለመተማመን ድርጅቱ እየፈረካከሱበት እንደሆነ እና ህዝቡ ዘንድ ያለውም ጥላቻ መስፋቱ ድንጋጠው እንዲበረታ ሲያደርጉት ከመሪው መለስ ሞት በኋላ መራባውያን በጥርጣሬ እያኡት መሆኑ ደሞ ስጋት ፈጥሮበታል:: ከመለስ ሞት በኋላ ነጻነታችንን እናገኛለን ብለው የነበሩት የግንባሩ አባል ድርጅቶች የህ/ማርያም ወደ ስልጣን መምጣት ስልጣናቸውን ለየክልላቸው ካለተጽእኖ እንደሚጠቀሙ እና ተሰሚነታችንም ከሕወሓት እኩ ይሆናል ብለው ቢገምቱን የመንግስቱ ስልጣኖች ሰፍተው እና አድገው በሕወሃት አመራሮች መያዛቸው ተስፋቸውን በማጨለሙ “ከሕወሓት የበላይነት ወደ እኩልነት የሚል እደምታ እንዲፈጠር ሆኗል:;
የኢሕኣዴግ አባላት እየተናቆሩ ያሉበት ያንድም ፓርቲ የማስወገድ ጥያቄ አሁንም ለማስቆም የወያኔ ጀሌዎች በካድረው ውስጥ ከፍተኛ ስራ እየሰሩ ቢሆንም ሊሳካላቸው አልቻለም:: የአንዱ ከፍታ እና የአንዱ ዝቅታ አሁንም ጥያቄው እንዳልተፈታ ነው: