Thursday, November 27, 2014

ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍ/ቤት የአፍሪካ መሪዎች ላይ ተጽእኖ እና ጫና እያደረገ ነው - ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ

http://www.djibtalk.com/ethiopia-prime-minister-accused-icc-of-intimidating-african-leaders-only/

ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍ/ቤት የአፍሪካ መሪዎች ላይ ተጽእኖ እና ጫና እያደረገ ነው - ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ
ጠቅላይ መኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት በአፍሪካዊያን መሪዎች ላይ ተጽእኖ እያደረገ ነው ሲሉ ወንጅለዋል፡፡
የአፍሪካ መሪዎችም የፍርድ ቤቱን ተግባር መቃወም እንቀጥላለን ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚንስትሩ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ በ11.4 በመቶ እድገት እያስመዘገበች ነው ብለዋል፡፡ በሀገሪቱ የባቡር መስመር ዝርጋታ እንዲሁም ሌሎች ፕሮጀክቶች እየተስፋፉ መሆናቸውን አስቀምጠዋል፡፡
ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለሱዳኑ ፕሬዝደንት ኦማር አል በሽር የእስር ትእዛዝ የጻፈ ሲሆን የኬንያው ፕሬዝደንት ኡህሩ ኬንያታም ባለፈው ፍርድ ቤቱ ባቀረበባቸው ክስ ባለፈው ሳምንት ፍ/ቤት መቆማቸው የሚታወስ ነው፡፡

Ethiopia: Prime minister Accused International Criminal Court (ICC)

Wednesday, November 26, 2014
DjibTalk News International / Djibouti
Hailemariam DesalegnAddis Ababa: Public Diplomacy and National security news. Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn defended his government’s policies and accused the International Criminal Court (ICC) of “intimidating” African leaders.
“Proof of this is the economic performance that made Ethiopia one of the fastest growing economies in the world,” Desalegn said at a parliamentary session. “In this fiscal year, our growth is projected at 11.4 percent, which surpasses the average 5-percent growth in the rest of Africa,” he said.
The Ethiopian premier said his country was implementing railway and manufacturing projects worth a total of $6.4 billion.
“The ongoing railway project, covering a total length of 2,095km, is the biggest of all the mega-projects in the country,” he said.
“So far, work on 1,500km of the stated project is well in progress in two corridors, the first one being the route from Addis Ababa to Djibouti and the other running from Mekelle to Awash [towns located to the north and east of the Ethiopian capital respectively],” Desalegn added.
Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn went on to say that funds for the project had been obtained from Turkey, Brazil, Russia and China, and from the government treasury. “However, the global economic crisis has delayed release of the funds,” he said, adding that seven out of ten planned sugar production factories would be built this year.
The Ethiopian premier said his government was committed to safeguarding the sovereignty of the country and fighting terrorism.
“There are anti-peace elements recruited by the Asmara government [in Eritrea] to implement its destructive plan. Some of them are hiding in the opposition camp, while others are caught serving such a government under the guise of journalism,” he said.
In this light, Desalegn said, it was the duty of the Ethiopian government to bring such “criminals” to court. Turning to the Ebola outbreak, which has killed thousands in West Africa, Desalegn said Ethiopia would participate in the global fight against Ebola, saying medical staff from the Ethiopian army would join their African counterparts in Ebola-hit countries.
Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn went on to accuse the ICC of “intimidating” African leaders.
“Our policy is clear from the outset – that the court is made to intimidate and harass African leaders,” he said. “We will continue to formally stand against it [the court] and will make our position known when the time comes.”
Last week, Kenyan President Uhuru Kenyatta appeared before the ICC at The Hague to answer charges of crimes against humanity. The ICC has also issued an arrest warrant for Sudanese President Omar al-Bashir for alleged war crimes and crimes against humanity in Sudan’s western Darfur province.


Wednesday, November 26, 2014

የህሊና እስረኞች ሳይቆጠሩ በእስረኞች ብዛት ኢትዮዽያ ከደቡብ አፍሪካ ቀጥላ ሁለተኛ አገር ሆና ተመዘገች

ኢንተርናሽናል ሴንተር ፎር ፕሪዝን ባካሔደው ጥናት በእስረኞች ብዛት ኢትዮዽያ ከደቡብ ኣፍሪካ ቀጥላ በሁለተኝነት ደረጃ ላይ እየመራች ሲሆን እንደ ሪፖርቱ ዘገባ እስከ ሚያዚያ ወር ድርስ ዘጠና ሶስት ሺ አርባ አርት እስረኞች ያስመዘገበች ሲሆን እስክሚቀለው ምርጫ ድረስ ደረጃውን አሻሽሎ አንደኛ ለመውጣት ጀግናው መንግስታችን ጠንክሮ በመስራት ላይ ይገኛል ።
በደቡብ ኣፍሪካ አብዛኛው በወንጀል አና በዝርፍያ የታስሩ እስረኞ ሲሆኑ እንደ ኢትዮጵያ የፖለቲካና በነፃነት ተናገርክ ተብሎ የታስረ የለም አናም ጀግናው መንግስታች ሆይ ታስሮ የተፈታን ገና የሚታስርን የታስረን አድርገህ ደርጃህን የማሻሻል አድል አለህና በርትተህ ልትሠራ ይገባልSouth Africa has recorded the highest number of prisoners in Africa, according to the International Centre for Prison Studies (ICPS).
According to the report, South Africa has recorded a total of 165 395 inmates in April 2014. This was followed by Ethiopia with 93 044 and Morocco with 72 816 prisoners.
The study revealed 2.3% of South Africa’s inmates in April were female, while 0.3% of the prisoners were minors.
There were 27.8% pre-trial detainees and 5.3% foreigners.
South Africa’s official capacity is 119 890 inmates, which means occupancy level is 127.7% over.
The report further found western African countries locked up 46 people per 100 000 population. In southern African countries this figure spiked to 205 people per 100 000 population.
Other significant findings were that almost half of the world’s prisoners are in the United States, China or Russia – countries which barely account for a quarter of the world’s population.
There are more than 10.2 million prisoners around the world.
“It is of grave concern that there are now over 10.2 million men, women and children held in penal institutions throughout the world. What is of graver concern is that the world prison population continues to rise, despite the fact that imprisonment is a highly expensive option for governments, as well as being inappropriate and ineffective for the majority of prisoners who come from minority and marginalised groups, or who are mentally ill or who are alcohol and drug abusers,” said the director of the ICPS, Peter Bennett.
“The International Centre for Prison Studies calls on those governments with high or rising rates of imprisonment to reduce their prison populations and to seek alternatives to custody in the interests of good economy, effectiveness in sentencing and the achievement of internationally agreed standards.”
photo credit: Thomas Hawk via photopin cc

Thursday, November 13, 2014

በጉግል የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት ማስጀመሪያ መመሪያ እና ለአማርኛ ቋንቋ ጦማሪያን ያለው አንድምታ





























  EFF
BY EVA GALPERIN

            በኢትዮጵያ የሚገኙ ጦማሪያን፡ ጋዜጠኞች እና የሰበአዊ መብት አራማጆች ከግዜ ወደ ግዜ እየተጠናከረ በሄደው የመንግስት የስለላላ መረብ እና የማስፈራሪያ ዘመቻ ኢላማ ሆነዋል:: መንግስት በባለቤትነት በያዘው የቴሌኮም አገልግሎት በመጠቀም የዜጎችን የመናገር እና የግላዊነት ነጻነትን ይተላለፍል:: በሀገር ውስጥ እና በውጪ የሚገኙ የተቃዋሚ ፓርቲ ድረ ገጾችን :የነጻ ሚዲያ አውታሮችን፡ጦማሮችን እና የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን በሀገር ውስጥ እንዳይነበቡ ማገድ የለት ተለት እውነታ ሆኗል::  በተጨማሪም ጋዜጠኞች፡ጦማሪያን እና የሰብአዊ መብት አራማጆች አስተየቶቻቸውን ከመንግስት አላማ ጋር እንዲያጣጥሙ እና ጽሁፎቻቸውን “ቀዝቀዝ” እንዲያደርጉ ማስፈራራት፡ ማጎሳቆል  ወይም ማሰር የተለመደ ክስተት ነው::

Wednesday, November 12, 2014

ቀለል ባለ አማርኛ በወያኔና በጭፍራዎቹ አመለካከት የዘረኞችና የግብዞቹን የወያኔን መንግስት መቃወም ማልት አምላክን እንደመስደብ አድርገው ይቆጥሩታል

 ቀለል ባለ አማርኛ በወያኔና በጭፍራዎቹ አመለካከት የዘረኞችና የግብዞቹን የወያኔን መንግስት መቃወም ማልት
                                             አምላክን  እንደመስደብ አድርገው ይቆጥሩታል

 
 ወያኔ ለኢትዮዽያና ለዜጎቿ ደንታ የሌለው ህዝቡን በመከፋፈል የጎጥና የሐይማኖት ጥላቻ በመስበክ ትውልዱን ራዕይ አልባ አድርጎ የሐገር ስሜት እንዳይኖረው በማድረግ እኔ ኦሮሞ እንጂ ኢትዮጵያዊነት አይገባኝም ጋንቤላዊ ካልሆነ ኢትዮጵያ ምንድን ነች አማራ ትግራይ ሀረሪ ጉራጌ እንጂ ኢትዮጵያ የምትሏት ምኔ ነች የሚል ትውልድ ማፍራት ና  ውስጥ ለውስጥ በአገዛዙ     እንደ  

  ፖሊሲ እየነደፈ ልዩነትን በማስፋፋት እርስ በርስ ከፍለው የነሱን ስርአት ለማራዘም ሲሞክሩ ማየት የተለመደ ሆኗል በተጨማሪም ካድሬዎቻቸው በደም የመጣ ስልጣን ነው አንዴት በምርጫ ብለው ይከራከራሉ ህዝቡ ነፃነቱን ተገፎ የሐገሪቱን
ሕዝብ በጎሣ በሐይማኖት እንዲጋጭ የተማረውንም ያልተማረውንም በጥቅማ ጥቅም ወይም በግዴታ የፓርቲው አባል በማድረግ
የተማረ ከሆነ ስራ ለማግኘት ወይም የስልጣን እርከን ለማሳደግ ያልተማረውን በኮንደሚኒየም ና በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች በማታለል ፍርድ ቤቶችና ሚድያዎችን መቶ በመቶ ለራሳቸው ጥቅም እንዲቆሙ ፓርላማውን እንደአሻንጉሊት በማድረግ
በሕዝቡ ላይ አንደፈለጉ የማንአለብኝነት ድርጊት መፈፀም ከጀመሩ አመታት ተቆጠሩ

 እናም ነፃነት  ከሌሎች የምንጠብቀው ወይም ማንንም ስጠን ብልን የማንጠይቀው ፈጣሪ ለእያንዳንዳችን ያደለን ሐብታችን ነው ነፃነት የምንሻ ይቺን አገር እንደ ሐገር እንድትቀጥል  የምንፈልግ አብዛኛው ለውጥ ፈላጊም የሚስማማበት ጉዳይ ቢኖር የችግሮቻችን መጠን ቢለያዩም ችግሩ ግን በዘር በጎሣ በፆታ በእድሜ ወዘተ ሳይል ችግሩ የእያንዳንዱን ቤት ማንኳኳቱ  ነው በተልይም  ደግሞ ፍትህ የተጠማው ነፃነቱን ተገፎ ተረግጦም  ያለውን በየስርቤቱም የሚማቅቀውን ሐገሩን ጥሎም የሚስደደውንም  አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ይህ ሁኔታ እስከ መቼ ነው የሚቀጥለው ብሎ   ዘረኛውን የወያኔ መንግስት በአንድ ላይ ሆነን ልንታገለው ይገባል
     እግዛብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ

ዳንኤል አምዶም  

Thursday, November 6, 2014

Ethiopia: Human rights campaigner says African Union should move headquarters out of Ethiopia

የአፍሪካ ህብረት መቀመጫነቱ ከኢትዮጵያ መነሳት እንደመፍትሄ
ጋዜጠኛና ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ የሆነው አንጎላዊው ራፋኤል ማርክስ በኢትዮጵያ ያለው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ገና የሚቀረው በመሆኑ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫነቱ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በሰብዓዊ መብት ጥበቃ የተሻለ ወደ ምትባል ሀገር መቀየር ይገባል ባይ ነው፡፡
ህብረቱ 53 የአፍሪካ ሀገራትን የሚወክል ቢሆንም በሰብዓዊ መብቶች ረገድ ምንም አልሰራም ተብሏል፡፡
በተጨማሪም ይህ የአንጎላ ዜግነት ያለው ጋዜጠኛና ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ በሚሊየኖች በሚቆጠሩ ዶላሮች መጭበርበር ላይ የምርምር ጋዜጠኝነት ስራ በመስራቱ ሞዛምቢክ ውስጥ እ.አ.አ በ2000 ስለተገደለው ሞዛምቢካዊ ጋዜጠኛ ያስታውሳል፡፡ ስታር ትሪብዩን እንደዘገበው

Monday, November 3, 2014

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ላለፉት 3 ወራቶች ያሰለጠናቸውን የአምስተኛ ዙር ታጋዮች አስመረቀ


አገራችን ኢትዮጵያ በጎጠኛውና በከፋፋዩ የፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝ መዳፍ ውስጥ ከወደቀችበት ጊዜ ጀምሮ የደረሰባትንና እየደረሰባት ያለውን ውርደትና መከራ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በመገርሰስ ወደ ክብር ለመለወጥ፤ ብሎም የናቋትን እና ያዋረዷትን ጉጅሌዎች በፍትህ ሚዛን ላይ እንዲቀመጡና ፍርዳቸውን እንዲያገኙ ማድረግን ቀዳሚ አላማው አድርጎ ወደ ዱር የከተተውና፤ በአገራችን የነገሰውን ፍጹም አምባገነናዊ አገዛዝ በሚገባው ቋንቋ ሁሉ ለማነጋገር እጅግ በዘመነ ሁኔታ እየተደራጀ የሚገኘው የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል 5 ዙር ታጋዮችን ሰኞ ጥቅምት 17 ቀን 2007 አ.ም ማስመረቁን ከህዝባዊ ሃይሉ የተላከልን መረጃ ያመለክታል።ተመራቂ ታጋዮቹ ላለፉት 3 ወራት በተከታታይ በወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ እና የመረጃ እና ደህንነት ትምህርቶች በበቂ ሁኔታ መሰልጠናቸው የተገለጸ ሲሆን በአሁኑ ሰአት ያለውን የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበና ወቅቱ የሚፈልገውን ቴክኖሎጅ በመጠቀም መረጃን መቀበልና ማስተላለፍን የጨመረም እንደነበር ተያይዞ ተጠቅሷል።
በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የህዝባዊ ሃይሉ ዋና አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ማሩ የህዝባዊ ሃይሉን ወቅታዊ አቋም በተመለከተ ሲናገሩ ‘’ህዝባዊ ሃይላችን በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ዘረኛና አፋኝ የወያኔ አገዛዝ ከህዝባችንና ከአገራችን ጫንቃ ላይ አስወግዶ በምትኩ ፍትሃዊ ና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ከተመሰረተ ጀምሮ ባለፉት ጥቂት አመታት በርካታ ስራዎችን በመስራት አሁን አስተማማኝ ድርጅታዊ አቋም ላይ ይገኛል’’ ሲሉ በምረቃው ስነ ስርአት ላይ ለተገኙት የክብር እንግዶች ተናግረዋል። ኮማንደር አሰፋ ማሩ አያይዘው እንደገለጹት ‘’ይህን የአምስተኛ ዙር ምርቃት ከቀደምቶቹ 4 ዙር ምርቃቶች የሚለየው የኢትዮጲያ ህዝብ አርበኞች ግንባር፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ እና የግንቦት ሰባት የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ተዋህደው ባንድ ድርጅታዊ ጥላ ስር ትግላቸውን አስተባብረው ለመታገል የሚያደርጉትን የውህደት ሂደት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ያደረሱበት ወቅት ላይ መደረጉ ነው ‘’ ሲሉ አስረድተዋል።
ኮማንደሩ በስተመጨረሻም ‘’ይህ የህዝባዊ ሃይላችን ስልጠና በግንቦት ሰባት ስም ከሚደረጉት ስልጠናዎች የመጨረሻው ይሆናል በማለት የገለጹ ሲሆን ለተመራቂ ታጋዮች ባስተላለፉት መልዕክት ‘’ስልጠና ላንድ ታጋይ የትግሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን በስልጠና ላይ ያገኛችሁትን ትምህርት በተግባር ለቆምንለት ዓላማ እና ተልዕኮ በቁርጠኝነት እንደምታውሉት ሙሉ እምነቴን እገልጻለሁ‘’ ካሉ በኋላ የአገርና የትውልድ ጠላት የሆነውን የፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝን ከኢትዮጵያ ምድር ጠራርገን ለማስወገድ በምናደርገው እልህ አስጨረሽ ትግል አብረን እንቁም፤ ሕዝባዊ ሃይላችንንም ተቀላቀሉ ሲሉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ወገናዊ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል በሀገር ውስጥ እንደማእበል እየገነፈለ ያለውን የአታግሉን የሕዝብ ጥያቄ በተደራጀና በተቀነባበረ መንገድ በተገቢው መልኩ ለማስተናገድ እንዲችል እንደ ድርጅት ከመቼው ጊዜ በላይ ራሱን እያደራጀና እያጠነከረ እንደሚገኝና ምቹ አታጋይ ተቋም ሆኖ ለመውጣት ሌት ተቀን እየደከመ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ቀደም በ 4 ተከታታይ ዙሮች በርካታ ታጋዮችን ማስመረቁን መዘገባችን አይዘነጋም።