በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በጋሞ ጎፋ ዞን ቁጫ ወረዳ የሚኖሩና በወረዳዋ የልማትና የማንነት ጉዳይ ላይ ጥያቄ
አንስተዋል የተባሉ ዘጠኝ የሀገር ሽማግሌዎች መታሰራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለፁ።
… ነዋሪዎቹ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በወረዳዋ ከልማትና ከማንነት ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያላቸው 22 ጥያቄዎችን
በመያዝ ከ2001 ጀምሮ በየደረጃው ለሚገኙ የደቡብ ክልል የአስተዳደር አርከኖች ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ
ባለማግኘታቸው ጥያቄአቸውን ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንዲሁም ለፌዴሬሽን ም/ቤት ቢያቀርቡም ተገቢውን
ምላሽ ማግኘት እንዳልቻሉ ገልፀዋል። በቅርቡም በድጋሚ ጥያቄአቸውን በመያዝ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ
አቅርበው ወደ ወረዳዋ ከተመለሱ በኋላ መጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በቁጫ ወረዳ ዋና ከተማ ሰላም በር ፖሊስ
ጣቢያ መታሰራቸውና ከመጋቢት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ ማረሚያ ቤት መዛወራቸውን ተናግረዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ከወረዳው አስተዳደር በላይ የወረዳውን ነዋሪ የማስተባበር ስራ በመስራታቸውም በአስተዳደሩና ሕዝቡ
መካከል ግንኙነቱ መቋረጡን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ተናግረዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ ከ25 ጊዜ በላይ
ለክልሉና ለፌዴራል የመንግስት አካላት ጥያቄአቸውን አቅርበው ምላሽ ባለማግኘታቸው የወረዳው ሕዝብ ልጆቹን
ወደትምህርት ቤት እንዳይልክ፣ ግብር መክፈል እንዲያቆም፣ የኢህአዴግ አባላት ጭምር ማናቸውንም የልማት መዋጮ
እንዳይከፍሉ፣ ሕዝቡ አስተዳደሩ በሚጠራው ስብሰባ እንዳይወጣ፣ ከወረዳው ርዕሰ ከተማ ሰላም በር ካድሬዎች ወደ ሌሎች
ቀበሌዎች በተሽከርካሪ እንዳይገቡ መንገድ በመዝጋት፣ ሞዴል አርሶ አደሮችን ጨምሮ አንድ ለአምስት አደረጃጀት መዋቅር
ስር ከተደራጁ አካላት ጋር ሕዝቡ እንዳይተባበር በማድረግ የወረዳው አስተዳደርና በነዋሪው መካከል ግንኙነቱ ሙሉ
በሙሉ እንዲቋረጥ ለማድረግ መቻላቸውና በአሁኑ ወቅትም አስተዳደሩ ግብር መሰብሰብም አለመቻሉን ቀደም ሲል በወረዳው
ነዋሪዎች አስተባባሪነት በተሰራው ትምህርት ቤት ተማሪዎች ትምህርት እንዲያቆሙ በማድረግ ጥያቄአቸውን ወደአጠቃላይ
ሕዝባዊ እምቢተኝነት እንዲያመራ ማድረጋቸው ለወረዳው ቅርበት ያላቸው ወገኖች ገልፀዋል።
አንስተዋል የተባሉ ዘጠኝ የሀገር ሽማግሌዎች መታሰራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለፁ።
… ነዋሪዎቹ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በወረዳዋ ከልማትና ከማንነት ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያላቸው 22 ጥያቄዎችን
በመያዝ ከ2001 ጀምሮ በየደረጃው ለሚገኙ የደቡብ ክልል የአስተዳደር አርከኖች ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ
ባለማግኘታቸው ጥያቄአቸውን ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንዲሁም ለፌዴሬሽን ም/ቤት ቢያቀርቡም ተገቢውን
ምላሽ ማግኘት እንዳልቻሉ ገልፀዋል። በቅርቡም በድጋሚ ጥያቄአቸውን በመያዝ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ
አቅርበው ወደ ወረዳዋ ከተመለሱ በኋላ መጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በቁጫ ወረዳ ዋና ከተማ ሰላም በር ፖሊስ
ጣቢያ መታሰራቸውና ከመጋቢት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ ማረሚያ ቤት መዛወራቸውን ተናግረዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ከወረዳው አስተዳደር በላይ የወረዳውን ነዋሪ የማስተባበር ስራ በመስራታቸውም በአስተዳደሩና ሕዝቡ
መካከል ግንኙነቱ መቋረጡን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ተናግረዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ ከ25 ጊዜ በላይ
ለክልሉና ለፌዴራል የመንግስት አካላት ጥያቄአቸውን አቅርበው ምላሽ ባለማግኘታቸው የወረዳው ሕዝብ ልጆቹን
ወደትምህርት ቤት እንዳይልክ፣ ግብር መክፈል እንዲያቆም፣ የኢህአዴግ አባላት ጭምር ማናቸውንም የልማት መዋጮ
እንዳይከፍሉ፣ ሕዝቡ አስተዳደሩ በሚጠራው ስብሰባ እንዳይወጣ፣ ከወረዳው ርዕሰ ከተማ ሰላም በር ካድሬዎች ወደ ሌሎች
ቀበሌዎች በተሽከርካሪ እንዳይገቡ መንገድ በመዝጋት፣ ሞዴል አርሶ አደሮችን ጨምሮ አንድ ለአምስት አደረጃጀት መዋቅር
ስር ከተደራጁ አካላት ጋር ሕዝቡ እንዳይተባበር በማድረግ የወረዳው አስተዳደርና በነዋሪው መካከል ግንኙነቱ ሙሉ
በሙሉ እንዲቋረጥ ለማድረግ መቻላቸውና በአሁኑ ወቅትም አስተዳደሩ ግብር መሰብሰብም አለመቻሉን ቀደም ሲል በወረዳው
ነዋሪዎች አስተባባሪነት በተሰራው ትምህርት ቤት ተማሪዎች ትምህርት እንዲያቆሙ በማድረግ ጥያቄአቸውን ወደአጠቃላይ
ሕዝባዊ እምቢተኝነት እንዲያመራ ማድረጋቸው ለወረዳው ቅርበት ያላቸው ወገኖች ገልፀዋል።