Thursday, April 4, 2013

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤቱታ ያቀረቡ የሀገር ሽማግሌዎች ታሰሩ

በዘሪሁን ሙሉጌታ
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በጋሞ ጎፋ ዞን ቁጫ ወረዳ የሚኖሩና በወረዳዋ የልማትና የማንነት ጉዳይ ላይ ጥያቄ
አንስተዋል የተባሉ ዘጠኝ የሀገር ሽማግሌዎች መታሰራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለፁ።
… ነዋሪዎቹ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ በወረዳዋ ከልማትና ከማንነት ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያላቸው 22 ጥያቄዎችን
በመያዝ ከ2001 ጀምሮ በየደረጃው ለሚገኙ የደቡብ ክልል የአስተዳደር አርከኖች ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ
ባለማግኘታቸው ጥያቄአቸውን ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንዲሁም ለፌዴሬሽን ም/ቤት ቢያቀርቡም ተገቢውን
ምላሽ ማግኘት እንዳልቻሉ ገልፀዋል። በቅርቡም በድጋሚ ጥያቄአቸውን በመያዝ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ
አቅርበው ወደ ወረዳዋ ከተመለሱ በኋላ መጋቢት 2 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በቁጫ ወረዳ ዋና ከተማ ሰላም በር ፖሊስ
ጣቢያ መታሰራቸውና ከመጋቢት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ ማረሚያ ቤት መዛወራቸውን ተናግረዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ ከወረዳው አስተዳደር በላይ የወረዳውን ነዋሪ የማስተባበር ስራ በመስራታቸውም በአስተዳደሩና ሕዝቡ
መካከል ግንኙነቱ መቋረጡን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ተናግረዋል። የሀገር ሽማግሌዎቹ ከ25 ጊዜ በላይ
ለክልሉና ለፌዴራል የመንግስት አካላት ጥያቄአቸውን አቅርበው ምላሽ ባለማግኘታቸው የወረዳው ሕዝብ ልጆቹን
ወደትምህርት ቤት እንዳይልክ፣ ግብር መክፈል እንዲያቆም፣ የኢህአዴግ አባላት ጭምር ማናቸውንም የልማት መዋጮ
እንዳይከፍሉ፣ ሕዝቡ አስተዳደሩ በሚጠራው ስብሰባ እንዳይወጣ፣ ከወረዳው ርዕሰ ከተማ ሰላም በር ካድሬዎች ወደ ሌሎች
ቀበሌዎች በተሽከርካሪ እንዳይገቡ መንገድ በመዝጋት፣ ሞዴል አርሶ አደሮችን ጨምሮ አንድ ለአምስት አደረጃጀት መዋቅር
ስር ከተደራጁ አካላት ጋር ሕዝቡ እንዳይተባበር በማድረግ የወረዳው አስተዳደርና በነዋሪው መካከል ግንኙነቱ ሙሉ
በሙሉ እንዲቋረጥ ለማድረግ መቻላቸውና በአሁኑ ወቅትም አስተዳደሩ ግብር መሰብሰብም አለመቻሉን ቀደም ሲል በወረዳው
ነዋሪዎች አስተባባሪነት በተሰራው ትምህርት ቤት ተማሪዎች ትምህርት እንዲያቆሙ በማድረግ ጥያቄአቸውን ወደአጠቃላይ
ሕዝባዊ እምቢተኝነት እንዲያመራ ማድረጋቸው ለወረዳው ቅርበት ያላቸው ወገኖች ገልፀዋል።

ዜጎችን ከቀያቸው መፈናቀል የገዢው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲና ለህዝብ ያለው ንቀት የሚያሳይ ነው።

(አብርሃ ደስታ፣ መቀሌ)
ህወሓት/ኢህኣዴግ ከሚከተለው ‘ኣብዮታዊ ዴሞክራሲ’ የተሰኘ የፖለቲካ ኣቅጣጫ (እነሱ ‘ርእዮተ ዓለም’
ይሉታል) ኣንፃር ‘የቡድን መብት’ ከ’ግል መብት’ ይቀድማል። በብዱን መብት እሳቤ መሰረት (በኣንቀፅ 39
የ’እስከመገንጠል መብት’ ታግዞ) ብሄሮች በየክልላቸው ያለ ሃብት (ለምሳሌ መሬት) በዋናነት እንዲቆጣጠሩ
ያስችላል።
በዚ መሰረትም ‘የሌላ’ ክልል ተወላጆች በ’ሌላ ክልል’ መሬት የማግኘት መብታቸው ሲነፈጉ ይታያል። የኣማራ
ተወላጆች ብዙ ግዜ ኑሮኣቸው ከመሰረቱበት ቀያቸው በኃልና…በግፍ ሲፈናቀሉ እያየን ነው። በቡድን መብት
መሰረት የኢትዮዽያ ሕጋዊ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው መኖርያ መሬት ሲከለከሉ ማየት እጅግ ያሳዝናል። በሌላ
በኩል በስልጣን ያለ ድርጅት (የራሱን ዜጎች እያፈናቀለ) መሬ ታችን ተቀባይነት በሌለው መንገድ ለዉጭ ዜጎች
ሲቸረችር ይታያል። ዜጎቻችን በገዛ መሬታቸው ባዕድ ሁነዋል ።
የሚገርመው ደግሞ ‘መሬት ኣይሸጥም ኣይለወጥም’ ከሚል ግራ የተጋባ ፍልስፍና መሬታችን ለውጭ ዜጎች የሚሰጠው በነፃ ሊባል
በሚችል ሁኔታ መሆኑ ነው። (በነፃ የሚሰጥበት ምክንያት መሬት ተሸጠ እንዳይባል ነው)። የኣማራ ተወላጆች ከቀያቸው መፈናቀል
የገዢው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲና ለህዝብ ያለው ንቀት የሚያሳይ ነው። ዜጎችን በማባረር (‘ሕጋዊ ያልሆኑ ኗሪዎች’ በሚል ስም) መሬት
ለውጭ ዜጎች ሲሰጥ እነዚህ የሌላ ሀገር ዜጎች እንዴት ‘ሕጋዊ’ ሆኑ???
ሰዎች ከቀያቸው በሃይል (በግፍ በዘርሓረጋቸው እየተለዩ) ሲፈናቀሉ (ሲባረሩ) የከፋ የሰብኣዊ መብት ጥሰት ነው። ዜጎቻችን (ወገኖቻችን)
ሲፈናቀሉ የሚደርሳቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማሕበራዊና ስነልቦናዊ ቀውስ (Helplessness) መገመት ኣይከብድም። ሁሉም ኢትዮዽያ
ሊተባበራቸው ይገባል፤ መንግስት ይህን ተግባሩ እንዲያቆም ተፅዕኖ ማድረግ ኣለብን።
እኛም እየተፈናቀሉ ካሉ ሰዎች ጎን መሰለፍ ያለብን ይመስለኛል። ምክንያቱም (1) ወገኖቻችን ናቸው። እኛ ኢትዮዽያውያን
ያልደረስንላቸው ማን መጥቶ ይረዳቸዋል? (2) ዛሬ በኣማራ ተወላጆች እየተፈፀመ ያለው ግፍ (ኣሁንኑ ካልቆመ) ነገ በእያንዳንዳችን
እንደሚፈፀም ማወቅ ይኖርብናል። (3) የማፈናቀል ተግባሩ የብሄር ፖለቲካ ችግር ኣባብሶ የጥላቻ ፖለቲካ ስር ሰዶ የኢትዮዽያ ሀገራችን
ኣንድነት የሚፈታተን ይሆናል።

“የ መለስ ዜናዊ ሚስጥሮች …..በተስፋዬ ገ/አብ”


“የ መለስ ዜናዊ ሚስጥሮች …..በተስፋዬ ገ/አ

በየእለቱ አዳዲስ ዜናዎች እንሰማለን። ለአብነት “ስዩም መስፍን በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነ” የሚለው ተራ ዜና ነበር። “ስዩም ተወረወረ” ብለን ያመንንም ነበርን። ስዩም ሌላ ተልእኮ እንደተሰጠው ለመረዳት፣ የቻይናና የወያኔን የንግድ ስምምነቶች ማስላትና አንዳንድ አንጓዎች ብቅ እስኪሉ መጠበቅ ያስፈልግ ነበር። አባይ ፀሃዬ የስኳርና የጨው ሚኒስትር ሆኖ ሲሾም ብዙ ስላቆች አንብቤ ነበር። የአባይ ፀሃዬን አንገት የስኳር ጆንያ ውስጥ በመክተት ያላገጡ ሜዲያዎችም ነበሩ። ሆኖም የስዩምም ሆነ የአባይ ምደባዎች ቀጣዩን የወያኔ ዋና ዋና እቅዶች ጠቋሚ ነበሩ። የስዩምን ሹመት ተከትሎ፣ የወያኔ ባለስልጣናት ልጆች ለትምህርት ወደ ቻይና ተላኩ። እነዚህን ልጆች በኮሚኒስታዊ አስተሳሰብ አደራጅቶ ማዘጋጀት የሽማግሌው የትርፍ ጊዜ ተልእኮ መሆኑ እየተሰማ ነው።
ወያኔ የጦር መሳሪያ በብዛት እየገዛና እያመረተ ነው።
ጦር መሳሪያ የማከማቸቱ እውነተኛ አላማ ምን ይሆን? በአባይ ጉዳይ የግብፅን ጦር ለመመከት? ይሄ የተበላ እቁብ ሆኖአል። ትግራይን ለመገንጠል ቆርጠው ወስነው፣ በሹክሹክታ እንደሚሰማው TDF (Tigray Defense Force) የተባለውን ይፋ ያልሆነ መስሪያ ቤት በምስጢር እያደራጁ ይሆን?
የህወሃት ሰዎች ትግራይ በጠላት ተከባለች ብለው ማመናቸው ወይም እንዲታመን መፈለጋቸው የችግሩ ማእከል ይመስላል። “እንደ እስራኤል በጉልበታችን መኖር እንችላለን” የሚለው ቅዠት ውስጥ የገቡት አምነውበት ነው ወይስ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ? ይህን በትክክል ማወቅ አይቻልም። ህዋሃት የትግራይን ህዝብ እንደመሸሸጊያ ሊያመቻቸው ካላሰበ በቀር፣ የትግራይ ህዝብ የጎረቤት ጠላት የለውም። ሊኖረውም አይችልም። በፍቅር የመኖር ሰፊ እድል እያለ ግጭት ብቻ ለምን አማራጭ ሆኖ ይቀርባል?
“ወያኔ ስልጣን ላይ ለመቆየት የቀረችው አንድ የማጭበርበሪያ ካርድ አሰብን በጦር ሃይል መያዝ ናት። የጦር መሳሪያ ማከማቸቱም ለዚያ ኦፕሬሽን ሊሆን ይችላል” እያሉ የሚተነትኑ፣ በተዘዋዋሪም የሚገፋፉ አሉ።

Tuesday, April 2, 2013

ለ አቶ አዲሱ ለገሰ የቀረበ የህልውና ጥያቄ ? ?



ለመሆኑ እርስዎ አማራ ነኝ ይላሉ ከዚያም አምራውን ወክለው ለ20 ዓመታት ፀረ-አማራ ፀረ- ኢትዮጵያ አገዛዝ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ ይዘው ይገኛሉ እናም የሕውሀት መሥራቾች እንደሚሉን ከቅድመ ደርግ በፊት የነበረውን የመላ የኢትዮጵያውያንን ተማሪዎች ንቅናቄ ፀረ ፊዳሊዝም ሣይሆን ለትግራይ ሕዝብ የበላይነት የነበረ ነው ይሉናል እርስዎም የታገሉለት ለዚሁ ነበር ?
እርስዎ የተወለዱት በሓረር ሁኖ ሳለ ግን እርስዎ ለምርጫ ለመወዳደር የምረጡት በበለሳ ወረዳ ዙይ-ዝሀየ አካባቢ ቆላ ሐሙሲት ነው ምክንያትዎ ግልጽ ነበር ?
ለምን ባማራው ክልል እንዲሆን ተደረገ ወይስ ባማራው ክልል ታማኝ ሎሌ የሚሆን ስለጠፋ ይሆን ?
ውድ የነፃ አውጭ አባት ነወትና ከርስዎ እውነት አይጠፋምና መልሱን በጉጉት እጠብቃለሁ
  •  በትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ምሥረት መርኀ ግብር ውስጥ አራት ነጥቦች በግልፅ ሠፍረዋል። ትግራይን ነፃ ለማውጣትና በሰላም የራሷ መንግሥት አቋቁማ እንድትኖር በቁጥር አራት የሠፈረው፤ በአማራው መቃብር ላይ የትግራይን የበላይነት እናቋቁማለን ይላል። ከዚህ መመሪያ ሌላው ነገር ሁሉ ይመነዘራል።
  • የአማራ መኖሪያ የሆኑትን የወገራ፣ የጠለምትና የዋግ ክፍሎች ወደ ትግራይ ከልሎ፤ የዚሁ ቦታ ነዋሪዎች የሆኑትን፤ ሀብታቸውን ዘርፎ እነሱን ከቦታቸው አፈናቅሎ አባሯቸዋል። የሱዳን ደንበሩንም እንዲሁ።
  • አማራው እስከዛሬ የበላይ ስለነበረ፤ ካሁን በኋላ ወደ ሥልጣን እንዳይመጣ በሩን ለአማራው መዝጋት አለብን ይላል። በተግባርም ፈፅሞታል።
  • አማራው ከየትኛውም የሀገሪቱ ክልል ተጠራርጎ ወጥቶ በሠጠነው ክልል ብቻ ተዘግቶ ይኑር ይላል ተግባራቸው። ይህም ደግሞ፤ ንብረታቸውን በመንጠቅ፣ በእስር በማንገላታት፣ በመግደልና በማባረር ተግብሮታል።
  • የአማርኛ ተናጋሪ የዩኒቨርሲቲ መምህራንን ከሥራቸው አባሮ፤ ሌላም ቦታ ሠርተው እንዳይበሉ አድርጓቸዋል። በየመሥሪያ ቤቱ የነበሩትን አማራዎች በተመሳሳይ መንገድ ከሥራ አፈናቅሏቸዋል።
  • ደርግን አማራ እያለና የደርግን አረመኔነት የአማራ አረመኔነት አድርጎ፤ አማራን የትግራይ ወገናችን እንዲጠላው ማድረጉ፤ አማራውን የትግራይ ወገናችን እንዲያጠፋው ሆን ብሎ ማዘጋጀቱ ነው። በትግራይ ትምህርት ቤቶች፤ ይህ የደርግን አማራ ብሎ ማስቀመጡ፤ ትምህርት ተብሎ እየተሠጠ ነው።
  • የአማራ ድርጅት ብሎ ባቋቋመው፤ “ብሔራዊ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ” እንኳን፤ የሌላ ክፍል ወገኖቻችንን የሆኑትን አባላት በአመራር አስቀምጧል።
  • የአማራው ክልል ብሎ ባካለለው ቦታ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ንብረት የሆነው EFFORT ቁልፍ የልማት ቦታዎችን ከመውሰዱም ሌላ፤ በክልሉ በሙሉ የበላይነት ያላቸው ትግሬዎቹ ናቸው።
  • በዚሁ ክልል ተብየው የተቀመጠው የአማራው ወገናችን፤ በማንነቱ እንዲያፍርና እንዲሸማቀቅ እየተደረገ፤ በያለበት በማንነቱ እየተሰደበና እየተዋረደ ይገኛል። ስድቡን እዚህ ማስፈሩ ማራባት ይሆናል።
  • በዚህ ሁሉ በሚደርስበት የዕለት ከዕለት በደል የተነሳ፤ ቦታውን ለቆ፣ ሀገሩን ጥሎ፣ ለበረሀ እንግልትና ለባህር አሣ ምግብ ሆኖ፤ ብልቶቹ እየተቸረቸሩበት፣ በውርደትና ሀፍረት እየተሸማቀቀ ለስደት የተዳረገው አብዛኛው የአማራው ወገናችን ነው።

የሌንጮ ለታ አዲሱ ትግል – እንዴት? “ከእንግዲህ የቀድሞው መንገድ አይሰራም”

የሌንጮ ለታ አዲሱ ትግል – እንዴት? “ከእንግዲህ የቀድሞው መንገድ አይሰራም”


ላለፉት አርባ ዓመታት ለኦሮሞ ህዝብ ነጻነት ሲታገል የቆየው ኦነግ አመራሮቹ ሲጣሉና ሲታረቁ መስማት የተለመደ ነው። የግለሰብ ጸብ የሚመስለው የድርጅት በሽታ ሲንጠው የቆየው ኦነግ በውል ባይታወቅም ተሰነጣጥቆ ለሰሚው ግራ የሚያጋባ ድርጅት ከሆነም ዓመታት ተቆጥረዋል። ስህተትን ገምግሞ የትግል አቅጣጫና ፕሮግራም ከመቀየር ይልቅ ጊዜው ባለፈበት አስተሳሰብ ባለበት ሲረግጥ እድሜውን የፈጀ ድርጅት እንደሆነ ተደርጎም ይወሰዳል።
ስለ ኦነግ ሲነሳ አብዛኞች በመገረም የሚናገሩትና ሚዛን የሚደፋው አስተያየት የሚሰነዘረው በድርጅቱ መከፋፈልና መበጣጠስ ሳይሆን ተለያይተውም አስመራን የሙጥኝ ያሉበት ምክንያት ነው። ኢህአዴግ ህጻን እያለ ሻዕቢያ እንዳሻው ይነዳው እንደነበር የሚያስታውሱ አስተያየት ሰጪዎች ከሽግግር መንግስት ምስረታ በኋላ ኦነግ አገር ለቆ እንዲወጣ መንገዱን የጠረገው ሻዕቢያ መሆኑንን በቁጭት ይናገራሉ።
ኢህአዴግ ለስልጣን አዲስ በሆነበት የጨቅላነት ዘመኑ፣ ኦነግ በታሪኩ ያልነበረውን ሰራዊት በመገንባት አስጨንቆት እንደነበር በመጠቆም በወቅቱ አስተያየት የሰጡ ኢህአዴግ በተለይም መለስ በሻዕቢያ በኩል ኦነግን ለመታረቅ አቅርበውት የነበረውን የሽምግልና ጥያቄ ኦነግ እንዳይቀበል ሰሚ ባያገኙም በአጽዕኖት ምክራቸውን ሰጥተው ነበር።
በኦነግ ታጣቂ ሃይሎችና በኢህአዴግ ሰራዊት መካከል እኩል ሊባል በሚችል ደረጃ የጡንቻ  መፈታተን ነበር። ደርግ ሲበታተን ኦነግን የተቀላቀሉ የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰራዊት አካላት ወያኔን የማዳፋት አቅሙ ነበራቸው። በወቅቱ የንስር ያህል ጉልበትና ሃይል ቢኖራቸውም ራሳቸውን ጫጩት አድርገው ተመለከቱ። አዲስ አበባ ሲገቡ የነበራቸውን የህዝብ ድጋፍ አራግፈው ጣሉት። በስሜት እየተነዱ ከሚወዷቸው ሁሉ ተቀያየሙ። ህወሃት አጋጣሚውን ለቅስቀሳና ለስም ማቆሸሻ ሰራበት። በስተመጨረሻ ኦነግ ሃይሉንና አቅሙን ዘንግቶ በአመራር ችግርና በአቋም ሸውራራነት ሃይሉን በሙሉ ወደ ካምፕ በማስገባት የኢህአዴግን የእርቅ ጥያቄ ተቀበለ። ሰራዊቱን እየነዳ በፈቃደኛት አሳሰራቸው።

In Aid to Ethiopia, a Costly Trade-Off April 1, 2013 Share toFacebook Twitter written by Chloe Schwenke Vice President of Global Programs

In Aid to Ethiopia, a Costly Trade-Off April 1, 2013 Share toFacebook Twitter written by Chloe Schwenke Vice President of Global Programs A Community consultation on a draft peace accord in Hudet, Somali Region, Ethiopia. Photo Credit: Mercy Corps The dividing line between developmental assistance and aid that is intended to strengthen human rights and democratic governance is an obscure boundary, yet it has considerable moral and strategic significance. Donor countries must weigh a variety of factors—including security and economic questions and the geopolitical role of the beneficiary country—that often leave democracy and human rights goals on the back burner. Such a ranking of priorities has an immediate negative effect on the ground, and it ultimately represents a costly trade-off in which long-term interests are exchanged for

Azib Mesfin VS Aba mela

Monday, April 1, 2013

በፌስ ቡክ አስተያየት የፃፈ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ታሰሩ !


በፌስ ቡክ አስተያየት የፃፈ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ታሰሩ !

በአዲሱ የአዲስ አበባ ቴክኒዎሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የሆነዉ ወጣት በዚሁ ምክንያት ታስሮ ወደአርባምንጭ መወሰዱን ወኪላችን የላከልን ዘገባ ያመለክታል። የአርባ ምንጭ ፖሊስ የሰዎች ስም የሚያጎድፍ በማዉጣቱ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከአዲስ አበባ ወስደን ለፍርድ ለማቅረብ ጉዳዩን እያጣራሁ ነዉ ማለቱንም ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር በዘገባዉ ጠቅሷል።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር  audio 

UN calls for Ethiopia journalist Eskinder Nega to be released

Ethiopia journalist Eskinder Nega remains imprisoned.

In an opinion released today by Freedom Now, the UN Working Group on Arbitrary Detention found the Government of Ethiopia’s continued detention of independent Ethiopian journalist and blogger Eskinder Nega a violation of international law. The panel of five independent experts from four continents held that the government violated Mr. Nega’s rights to free expression and due process. The UN Working Group called for his immediate release.
Mr. Nega is serving an 18-year prison sentence on terror and treason charges in response to his online articles and public speeches about the Arab Spring and the possible impact of such movements on the political situation in Ethiopia. Arrested in September 2011, Mr. Nega was held without charge or access to an attorney for nearly two months before authorities charged him under Ethiopia’s widely criticized anti-terror laws. This is the eighth time during his 20-year career as an independent journalist and publisher that the Ethiopian government has detained Mr. Nega. His appeal has been repeatedly postponed, most recently on March 27, 2013.
In the attached opinion, released in conjunction with an op-ed by the renowned Ethiopian opposition leader and former prisoner of conscience Birtukan Mideksa, the UN Working Group found that the application of overly broad anti-terror laws against Mr. Nega constituted an “unjustified restriction” on his right to freedom of expression. The UN Working Group’s opinion also recognized “several breaches of Mr. Nega’s fair trial rights,” further rendering his continued detention arbitrary under international law.
“The Ethiopian government cannot continue to use anti-terrorism legislation to muzzle the work of independent journalists, even when it does not like what is being reported,” said Freedom Now Executive Director Maran Turner. “The targeting of journalists by resorting to overly broad anti-terror laws, just like the use of anti-state charges in the pre-9/11 era, is a violation of the internationally protected right to free expression and undermines international efforts to address real security threats.”
Freedom Now represents Mr. Nega as his international pro bono counsel.
** Freedom Now sent this statement to Bikyanews.com

አማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ አካል ነዉ! (ግንቦት 7) መግለጫ ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ

አማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ አካል ነዉ! (ግንቦት 7) መግለጫ ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ Click here for PDF የወያኔ መሪዎች እነ መለስ ዜናዊና ስብሐት ነጋ በ1967 ዓም ለትግል ደደቢት በረሀ እንዲገቡ ያነሳሳቸዉና ያሰባሰባቸዉ በአማራዉ ህዝብ ላይ ያላቸው ጥላቻና የበቀል ስሜት እንጂየኢትዮጵያ ህዝብ በደልና እሮሮ አንገፍግፏቸዉ እንዳልሆነ በተለያዩ ግዜዎች ለህዝብ ይፋ የሆኑት የወያኔ መግለጫዎችና ለረጂም ግዜ ወያኔን የመሩት መለስ ዜናዊና ስብሐት ነጋ በየአደባባዩ ላይ ያደረጓቸዉ ንግግሮች በግልጽ ያሳያሉ። እነዚህ ከወጣትነት ግዜያቸዉ ጀምሮ በአማራ ህዝብ ላይ ጥርሳቸዉን የነከሱ የወያኔ መስራቾች በለስ ቀንቷቸዉ አዲስ አበባን ከተቆጣጠሩ በኋላም ቢሆን ለአማራ ህዝብ፤ ባህልና ታሪክ ያለቻዉ ጥላቻ ከተራ ጥላቻ አልፎ በተግባር አማራዉን ወደ ማጥቃት ዘመቻ አደገ እንጂ ለአንድም ቀን ቀንሶ አያውቅም። የወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያ ውስጥ ያከበረዉ ወይም የኤኮኖሚና የፖለቲካ ጥቅሙን ያስጠበቀለት ብሔረሰብ ባይኖርም በግለሰብ ደረጃም ሆነ በቡድን የወያኔ ዘረኞች የአማራን ህዝብ ከተቀሩት ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹና እህቶቹ ነጥለዉ ለማጥቃትና የስነ ልቦና ዘይቤውን ለመስበር ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። በአጠቃላይ የወያኔ ዘረኛ ባለስልጣኖች አማራውን በተከታታይ ሲዘልፉ ቆይተዋል፤አዋርደው አስረዋል፤ ከአገር እንዲሰደድ አድረገዋል፤ አፈናቅለዋል ገድለዋል። ለምሳሌ ወያኔ ስልጣን በያዘባቸዉ በመጀመሪያዎቹ አምስት አመታት ዉስጥ ብቻ አሶሳ፤ በደኖና አርባጉጉ ውስጥ አማራ በመሆናቸዉ ብቻ ህጻናት፤ሴቶችና አረጋዉያን በግፍ ተገድለዋል። ባለፈዉ አመት በደቡብ ክልል ጉራ ፈርዳ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ለረጂም አመታት ከአካባቢዉ ኢትዮጵያዊ ወገናቸው ጋር ተግባብተዉ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች አማራ በመሆናቸዉ ብቻ ለአመታት ያፈሩትን ንብረት ይዞ የመሄጃ ግዜ እንኳን ሳይሰጣቸዉ አከባቢዉን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለቅቀዉ እንዲወጡና እንዲፈናቀሉ ተደርጓል።

ዕውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው?

ዕውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው? የኢትዮጵያ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽ ኮሚቴና ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በመሆን ያዘጋጁት ሰላማዊ ሰልፍ አላማ ለፋሺስቱና ለጦር ወንጀለኛው ግራዚያኒ በጣሊያን ሀገር የተገነባውን መናፈሻ ስፍራና ሀውልት ለመቃወም ነው፡፡ ይህ ግለሰብ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ ታሪክ አይዘነጋውም፡፡ ግራዚያኒ በመርዝ ጋዝ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ጨፍጭፏል፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ ለቀናት በዘለቀው የበቀል ጭፍጨፋም በአካፋ ሳይቀር በአዲስ አበባና በአካባቢዋ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በግፍ ጨፍጭፏል፡፡ ግራዚያኒ በወቅቱ በሰጠው ትዕዛዝ የፋሺስት ወታደሮች ህይወት ያለውን ተንቀሳቃሽ ፍጥረትን ሁሉ ገድለዋል፡፡ ይህ እሩቅ በማይባል ጊዜ የተፈፀመ ድርጊት ነው፡፡ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ለእንዲህ አይነቱ ጨፍጫፊ የተገነባን ሀውልት ለመቃወም በወጡ ዜጎች ላይ የወሰዱት የእስር ተግባር እውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው? አስብሎናል፡፡ ኢህአዴግ በስልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ በተደጋጋሚ ጥፋት ፈፅሟል፡፡ ሀገራችንን የባህር በር ማሳጣትን ጨምሮ ሀገራዊ ስሜትን አንኳሶ ጠባብ የብሔር ስሜት እንዲንሰራፋ አድርጓል፣ ታሪክን ለስልጣኑ መደላድል ሲል በራሱ መንገድ የሚያዘጋጀው የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያን ጠፍጥፎ እንደሰራት ሁሉ ደርግን ለመጣል ካደረገው ትግል ውጪ ያለውን የአርበኞች ተጋድሎ እውቅና ሲሰጥ አይታይም፡፡ መንግስት ለፋሽስቱ ሩዶልፍ ግራዚያኒ የተገነባውን ሀውልት በመቃወም የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ ሳያንስ ግራዚያኒን ለማውገዝ የወጡ ዜጎችን በመደብደብና በማንገላታት ማሰሩ አሳፍሮናል፡፡ ለዜጎቻቸው እና ለሚመሯት ሀገር ክብር የማይሰጡ ይልቁንም የጦር ወንጀለኛና ፋሺስትን ለመቃወም የወጣን ዜጋ ማሰርራቸው የኢህአዴግ ባለስልጣናት ወገንተኝነታቸው ለዜጎቻቸው ነው ወይስ ለፋሺስት? የሚል ዘግናኝ ጥያቄ እንድንሰነዝር ያስገድደናል፡፡ በሰልፉ ላይ የተገኙት ሀገር ወዳድ ዜጎች በማን አለብኝነት ሲታሰሩ ድባደባ ተፈፅሞባቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የታሳሪዎቹን የኢሜይልና የማህበራዊ ገፅ የይለፍ ቃል (password) በግዳጅ የሚቀበሉ የደህንነት ሀይሎች ተልከውባቸዋል፡፡ ይህን ቅጥ ያጣ አንባገነናዊ ድርጊት የፈፀመው ወይም እንዲፈፀም ትዕዛዝ የሰጠው አካል ማንነት ተጣርቶ የማስተካከያ እርምጃ ሊወሰድ ይገባዋል፡፡ በየምክንያቱ ዜጎችን ማሰር የለመደው አንባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት ምን ያክል ኢትዮጵያዊነትን እየተዋጋ እንዳለም የሚያሳይ ድርጊት ነው፡፡ መሰረቱ ዜጎች በማንኛውም ጉዳይ ላይ የተቃውሞም ሆነ የድጋፍ ሰልፍ ማድረግ እንደሚችሉ

Explosive response to the genocide(ethnic cleansing) of Amharas in Ethiopia

Time to be united and pay all the price to overthrow this racist group to save our country. The Amhara people fight together with others to overthrow previous regimes but now woyane has the support of more than 98% tigrie people. This banda regime must pay the price.

Horrifying video of Ethiopian refugees being beaten by their Arab captives in Saudi Arabia

አዜብ እርግጫሽ አልበዛም? ይነጋል በላቸው

አዜብ እርግጫሽ አልበዛም? ይነጋል በላቸው ከሰሞነኛ አስቂኝ ዜናዎችና ሀተታዎች አንዱ የወይዘሮ አዜብ ድህነት ነው፡፡ ‹ባለቤቴ መለስ የባንክ ደብተር ያልነበረው፣ ቤተሰቡን በአራት ሺህ ብር ገቢ ብቻ በችጋር የሚቆላ፣ መላ ሕይወቱን ለእናት ድርጅቱ ለሕወሓትና ለኢትዮጵያ ሲል መስዋዕት ያደረገ …› እያለች ታወራለች አሉ፤ ‹ወጣ ብሎ በትርፍ ሰዓት እያስተማረ እንዳይደግፈን የፀጥታው ሁኔታ አላመቸውም› ብላ አለመጨመሯም እርሷው ሆና ነው – ‹የመለስ አንጎል በበማርኬት ጨረታ በሚሊዮን የሚገመት ሸያጭ ያወጣል› ስትል ቅንጣት ያላፈረች ወራዳ ሴት እኮ ናት፡፡ እኔም ሰው አገኘሁ ብዬ ስለርሷ ጊዜየን ማጥፋቴ እየከነከነኝ ነውአ- አሁን፤ ልፋ ያለው እንዲሉ ነው፡፡ ቀደም ሲልም ‹መለስ ጥሎብኝ የሄደውን የጋራ ልጆቻችንን በማሳደግ እፈተናለሁ› ብላ ነበር አሉ፡፡ የማትለው ነገር የለም ይባላል ይቺ የጉድ ተራራ – ሦስተኛይቱ ዮዲት ጉዲት፡፡ የውሸታም ልጅ ውሸታም ነው መቼም፤ የቀዳዳው መለስ አባትም – አጥንቱን መሬት አትመቸውና – ያ ዜናዊ የሚሉት የሀገር ነቀርሣ – ‹ ልጄ መለስ የገንዘብን ትርጉም አያውቅም፡፡ የዐሥር ብርን ኖት ከአምስት ብር ለይቶ አያውቅም፡፡…› ብሎ ነበር በ97 አካባቢ ለአንድ መጽሔት በሰጠው ቃለ መጠይቅ፡፡ የተረገመ ቤተሰብ እርግማኑ ሁለንተናዊ ነው፡፡ እነዚህ የባንዳ ልጆች – መለስም አዜብም ውሸታሞችና ልቅ አፎች ናቸው – ለከት ብሎ ነገር አልፈጠረባቸውም፤ ግን ግን እስኪ አስቡት – ኃጢያታችን እንዴት ቢከፋ ይሆን ከ90 ሚሊዮን ሕዝብ መካከል ሀገር የሚመራ ደህና ሰው ጠፍቶ ለነዚህ አጋንንት አሳልፎ የሰጠን አያቷ ደጃች ጎላ የዳጃማችነት ሹመቱን ከጣሊያን በባንዳነት እንዳገኙት ሰምቻለሁ፡፡ የመለስ አባትም ሚስት እንኳ እንዳያገኝ አገር በሤራ የረገመው ከሃዲ ባንዳ እንደነበር የታወቀ ነው፡፡ ከእነዚህ እርጉማን ምንም ዓይነት መልካም ነገር እንደማይጠበቅ ግልጽ ነው፡፡

April 1, 2013 - For Immediate Release - Also read the UN General Assembly Report – WGAD Opinion UN FINDS IMPRISONMENT OF ETHIOPIAN JOURNALIST ESKINDER NEGA ARBITRARY UNDER INTERNATIONAL LAW AND CALLS FOR IMMEDIATE RELEASE

April 1, 2013 - For Immediate Release - Also read the UN General Assembly Report – WGAD Opinion UN FINDS IMPRISONMENT OF ETHIOPIAN JOURNALIST ESKINDER NEGA ARBITRARY UNDER INTERNATIONAL LAW AND CALLS FOR IMMEDIATE RELEASE Washington, D.C.: In an opinion released today by Freedom Now, the UN Working Group on Arbitrary Detention found the Government of Ethiopia’s continued detention of independent Ethiopian journalist and blogger Eskinder Nega a violation of international law. The panel of five independent experts from four continents held that the government violated Mr. Nega’s rights to free expression and due process. The UN Working Group called for his immediate release. Mr. Nega is serving an 18-year prison sentence on terror and treason charges in response to his online articles and public speeches about the Arab Spring and the possible impact of such movements on the political situation in Ethiopia. Arrested in September 2011, Mr. Nega was held without charge or access to an attorney for nearly two months before authorities charged him under Ethiopia’s widely criticized anti-terror laws. This is the eighth time during his 20-year career as an independent journalist and publisher that the Ethiopian government has detained Mr. Nega. His appeal has been repeatedly postponed, most recently on March 27, 2013. In the attached opinion, released in conjunction with an op-ed by the renowned Ethiopian opposition leader and former prisoner of conscience Birtukan Mideksa, the UN Working Group found that the application of overly broad anti-terror laws against Mr. Nega constituted an “unjustified restriction” on his right to freedom of expression.