Monday, April 8, 2013

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለ3ኛ ጊዜ ህትመቱ ተቋረጠበት


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለ3ኛ ጊዜ ህትመቱ ተቋረጠበት


3 ጊዜ ህትመቱ የተቋረጠበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ” ከእንግዲህከጫካ መለስ ባሉ መታገያ መንገዶች በመጠቀም መብታችን እናስከብራለንአለ
እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይህን የተናገረው ልእልና ጋዜጣበመንግስት ጫና እንዳድታተም ከታገደች በሁዋላ ነው። ጋዜጠኛ ተመስገን ”የንግድ ሚኒስቴር በልእልና ጋዜጣ የቀድሞ ባለቤትና በአዲሱ ባለቤትመካከል ህገወጥ የሆነ የስም ዝውውር ተደርጓል በማለት የንግድ ፈቃዱ  ”እንዲሰረዝ መደረጉን ተነግሯል።
ፍትህ ጋዜጣ በህገወጥ መንገድ እንዳይታተም ከተደረገ በሁዋላ፣ ጋዜጠኛውአዲስ ታይምስ መጽሄትን ከሌላ አሳታሚ ላይ በመግዛት ለተወሰኑ ሳምንታትሲያሳትም ቆይቷል።
መጽሄቷ በተመሳሳይ መንገድ እንድትዘጋ ከተደረገ በሁዋላ፣ ጋዜጠኛተመስገን እንደገና ልእልና ጋዜጣን ከሌላ አሳታሚ ላይ በመግዛት ስራውንለመስራት ሞክሮ ነበር። ይሁን እንጅ 100  ብር በላይ በሆነ ወጪየገዛው ጋዜጣ  ከመንግስት በተላለፈው ጫና እንዳይታተም በድጋሜታግዶበታል
ተመስገን በራሱ ስም ፈቃድ አውጥቶ መስራት ከተከለከለ፣ ከእንግዲህ ወዲያስለሚኖረው አማራጭ ሲጠየቅ፣ “ያለኝ አማራጭ ከሲቪክ ተቋማት ጋርበመተባበር  ከጫካ ትግል በመለስ ያሉትን የሰላማዋ ትግል አማራጮችበመጠቀም  አስገዳጅ ሁኔታ በመፍጠር መብታችንን እናስከብራለንብሎአል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ሰሞኑን በገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ከፍተኛ ወከባሲደርስበት እንደነበር  ይታወሳል።  ተመስገን፣ 106 ያላነሱ ክሶችምእንዳሉበት ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment